የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ዐበይት የሥራ ክንውኖችና አባታዊ መመሪያዎች
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በቅዱስ ፓትርያርክነት ሥልጣን ከተሠየሙበት ጊዜ አንሥቶ እስከ አሁን ድረስ እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ በቅዱስ ሲኖዶስ እያስወሰኑ ለቤተ ክርስቲያናችን በርካታ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች መቀላጠፍ ዐይነተኛ ጠቀሜታ ያላቸው መመሪያዎችን አስተላልፈዋል፡፡
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
መድኀኔ ዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላካዊ የማዳን ሥራውን ወደ ዓለም እንዲያዳርሱ ዐሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርትን ከዐሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል መርጦ ለሦስት ዓመት ከአራት ወር ከዐሥር ቀን አምላካዊ ትምህርተ ወንጌልን አስተምሮአቸዋል፡፡ ከዋለበት እየዋሉ ካደረበት እያደሩ አምላካዊ ትምህርቱን ሰምተው፣ መለኮታዊ ገቢረ ተኣምሩን አይተው፣ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑን ተረድተዋል፡፡ (ዮሐ. 6) ካመኑ በኋላ “ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ፤ ያመነ የተጠመቀ ይድናል@ ያላመነ ግን ይፈረድበታል”፡፡ (ማር.16፥15-16) ብሎ አዘዛቸው፡፡ በክርስትና ትምህርት ይህ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ የሰጠው ወንጌልን ለዓለም ሁሉ የማስተማር (የመስበክ) ተልእኮ “ዐቢይ ተልእኮ” (great mission) ተብሎ ይጠራል፡፡
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት የተከበረው የጸሎተ ሐሙስ በዓል እንደተለመደው በጾም፣በጸሎት፣ በኅጽበተ እግር ሥነ ሥርዐትና በሥርዐተ ቅዳሴ ተከብሯል፡፡ሙሉ ሥነ ሥርዐቱ በቅዱስ ፓትርያርኩ የተመራ ሲሆን ቀኑ የትሕትና የፍቅር ስለሆነ ይህንን የጌታችን የአምላካችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትሕትና ተግባር ሁሌም ከልባችን ጽላት ላይ በመጻፍ ምእመናን የሕይወታቸው መርሕ እንዲያደርጉት አሳስበዋል፡፡



ከጥቅምት 12 እስከ 26 ቀን 2007 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡
ምልአተ ጉባኤው ከጥቅምት 12-26 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ ባደረገው ምልአተ ጉባኤ በተመረጡ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትና የሕግ ባለሙያዎች ሲደከምበት የቆየውን የተሻሻለውን ሕገ ቤተ ክርስቲያን አጽድቋል፡፡ በ33ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተወያይቶ ባጸደቀው የዐቋም መግለጫና በሌሎችም በርካታ ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች ላይ በስፋትና በጥልቀት ሲወያይ ከሰነበተ በኋላ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ስብሰባውን በጸሎት አጠናቋል፡፡
ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
ቤተ ክርስቲያንን በንጹሕ ደሙ የዋጀ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምእመናንን በቅዱስ መንፈሱ መሪነት እየጠበቀ ከዚህ ጊዜ ስላደረሰን ክብርና ምስጋና ለእርሱ እናቀርባለን፡፡
33ኛው ዓመታዊ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከጥቅምት 5-8 ቀን 2007 ዓ/ም አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡
“እንኳን ወደዚህ ታላቅ ጉባኤ መጣችሁ፣ እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ”
መስከረም 16 ቀን የ2007 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
በመስቀል ላይ በተከፈለው መሥዋዕትነት የሰውን ልጅ ከኀጢአት ፍዳ የታደገ ጌታችንና አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለ2007 ዓ.ም በዓለ መስቀል አደረሳችሁ፡፡
መስከረም 1 ቀን የ2007 ዓ.ም የዘመን መለወጫ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
“ወዓመቲከኒ ዘኢየኃልቅ — ዘመንህም አያልቅም።»
(መዝ 101÷27)
ነሐሴ 1 ቀን የ2006 ዓ.ም የጾመ ፍልሰታ መግቢያ ቃለ በረከት!
“ወዘሰ እንተ አንቀጽ ይበውእ ኖላዌ ዐባግዕ ውእቱ
በበሩ የሚገባ የበጎች እረኛ ነው።
(ዮሐ. 10፥2)
ከግንቦት 6-19 ቀን 2006 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች
የመክፈቻው ሥርዐተ ጸሎት ከተፈጸመበት ከበዓሉ ዋዜማ ከግንቦት 5 ቀን 2006 ዓ.ም.ጀምሮ እስከ ግንቦት 19 ቀን 2006 ዓ.ም. ለ16 ቀናት ባደረገው ጉባኤ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለኅብረተሰቡ የሚጠቅመውን፤ ለሀገርና ለዓለም ሰላም የሚበጀውን አጀንዳ በማመቻቸት በስፋትና በጥልቀት ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ከተላለፉት ውሳኔዎች መካከል ዋናዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡
ግንቦት 6 ቀን 2006 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
“ወንሩጽ በትዕግሥት ኀበ ዘጽኑሕ ለነ ተስፋነ ዘሃይማኖት ተጠብቆልን ወዳለ ተስፋ ሃይማኖት ለመድረስ በትዕግሥት እንሩጥ” (ዕብ. 12፥1)
ሚያዝያ 12 ቀን የ2006 ዓ.ም በዓለ ትንሣኤ
እርሱ ሕያው ሆኖ ሕያዋን መሆናችንን በትንሣኤው ላበሠረን ለጌታችን ለአምላካችንና ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ እንኳን በሰላም አደረሳችሁ!! ‹‹ወርኢናሃ ለሕይወት፤ ወተዐውቀት ለነ — ሕይወትን አየናት፣ አወቅናትም›› (1ዮሐ. 1÷2)
የካቲት 16 ቀን የ2006 ዓ.ም ዐቢይ ጾምን አስመልክቶ ያስተላለፉት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
‹‹ወእመሰ በምግባረ መንፈስ ቀተልክምዎ ለምግባረ ነፍስትክሙ ተሐይዉ ለዓለም፤ በመንፈሳዊ ሥራ ሥጋዊ ሥራችሁን ብትገድሉ ለዘለዓለሙ ትድናላችሁ›› (ሮሜ 8÷13)፡፡