• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

ቤተ ክርስቲያንን በንጹሕ ደሙ የዋጀ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምእመናንን በቅዱስ መንፈሱ መሪነት እየጠበቀ ከዚህ ጊዜ ስላደረሰን ክብርና ምስጋና ለእርሱ እናቀርባለን፡፡ እንደዚሁም ሁላችንን የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ከየሀገረ ስብከታችን በረድኤት ስቦ በሀብት አቅርቦ በዚህ ሐዋርያዊና ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ተገናኝተን በእግዚአብሔር ስለተሰጠን ዐቢይ ተልእኮ እንድንመካከር ስለሰበሰበን ስሙ የተመሰገነ ይሁን፡፡

‹‹ወመጺኦ ውእቱ መንፈሰ ጽድቅ ይመርሐክሙ ኀበ ኵሉ ፍኖተ ጽድቅ፤ ያ ሁላችንም እንደምናውቀው ይብዛም ይነስ፤ ዘመን ያለ ታሪክ አያልፍም፤ በየዘመናቱ ያለ ትውልድ በይበልጥ ደግሞ በኀላፊነት የሚቀመጡ ኀላፊዎች የታሪኩ አካል መሆናቸው አይቀርም፤ እንደሌላው ሁሉ እኛም ከዚህ እውነታ ማምለጥ አንችልም፡፡

ታሪክ አንድን ትውልድ በመልካም ወይም በመጥፎ ሊመዘግብ ይችላል፤ የእኛ ታሪክ እየተመዘገበ ያለው ከሁለቱ በየትኛው ነው? የሚለው ግን የሁላችንም መሠረታዊ ጥያቄ ሊሆን ይገባል፤ ይህንን ጥያቄ ለመመለስ ሩቅ መጓዝና ልዩ ምሁርን መጠየቅ አያስፈልገንም፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ ‹‹እስመ ኢኮነ ርሕ እምኔነ፤ ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም›› እንዳለው የሰው ኅሊና በአካባቢውና በውስጡ ያለውን ለይቶ ማወቅ ይቅርና ከአእምሮ በላይ የሆነውን የረቂቅ አምላክ ህልውና እንኳ በመጠኑም ቢሆን ማወቅ የሚችል ነው፡፡ (ዮሐ.ሥራ 1፥27)

መንፈስ ቅዱስም ‹‹ዮም አመ ሰማዕክሙ ቃሎ ኢታጽንዑ ልበክሙ ‹ዛሬ ድምፁን በሰማችሁ ጊዜ ልባችሁን አታጽኑ›› እያለ የሚጣራበት ጊዜ እንደሆነ ማወቁ አይከብድም››:: (ዕብ. 3፥15) በመሆኑም ራስን በራስ በመጠየቅ የሚገኝ መልስና ራስን በራስ በመወሰን የሚሰጥ ዳኝነት ከሁሉም የበለጠ ፈዋሽ መድኀኒት ነውና በራሳችን ዳኝነት የቤተ ክርስቲ ያናችንን ሉዓላዊነትና አንድነት እንደዚሁም ምእመናንዋና ሀብቷ የሚጠበቁበት ሥራዎችን መሥራት የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ ተግባር ነው፡፡

ታላቋና መተኪያ የማይገኝላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ በውስጥም ሆነ በውጭ የተጋረጡባት ግልጽና አደገኛ ፈተናዎች እንዳሉ መገንዘብ አለብን፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ከሚታዩ ፈተናዎች አንዱና ዋነኛው በሚሊዮን የሚቈጠሩ ምእመናን ወደ ሌላ እምነት እየፈለሱ ከመሆናቸው ሌላ፤ የቤተ ክርስቲያናችን ሀብትና ንብረት አያያዝ አስተማማኝ ሆኖ አለመገኘቱ፤ የሰው ኀይል፣ የገንዘብና የንብረት አስተዳደራችን በዘመኑ ቴክኖሎጂ የተቃኘ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፈነ አለመሆኑ፤ በቤተ ክርስቲያን ስም ቤተ ክርስቲያን የማታውቀውና የማትቈጣጠረው ሀብትና ንብረት የሚሰበስቡ ማኅበራት እየተበራከቱ መምጣታቸው፤ በቤተ ክርስቲያን ስም ሀብትን የሚሰበስቡ ማኅበራት በእነርሱ የምትተዳደር ቤተ ክርስቲያን ሳትኖር የቤተ ክርስቲያን ብቸኛ መብት የሆነውን ከምእመናን ገንዘብና ንብረት የመሰብሰብ ሥልጣንን ወደራሳቸው በማዞር ገንዘብና ንብረት ከምእመናን መሰብሰብ መልመዳቸው፤ በዚህም ምክንያት በአንዲት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሁለት የተለያዩ ዐሥራትና በኵራት ሰብሳቢዎች እየተፈጠሩ መምጣታቸው፤ በቤተ ክርስቲያን እየተፈጠረ ያለው ሁለተኛ ባለሀብት ማኅበር በሂደት ቤተ ክርስቲያንን ወደ ሁለት የመክፈል አዝማሚያ እንዳለው ግልጽ ማስረጃ መገኘቱ፤ ማኅበራቱ በመንግሥትና በቤተ ክርስቲያን የማይታወቅ ሀብት የሚሰበስቡ በመሆናቸው ገንዘቡ በሚያስከትለው ሌላ ጉዳት ቤተ ክርስቲያን በአክራሪነት የምትፈረጅበት አጋጣሚ መከሠቱ፤ ማኅበራት በሌላቸው ሥልጣን በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ ሥራ በቀጥታ ጣልቃ እየገቡ የሰላም ጠንቅ ሆነው መገኘታቸው፤ ችግሩን በቀላሉ ለማስተካከል ቢሞከር እንኳ ማኅበራቱ ከቤተ ክርስቲያኒቱ የሚሰ ጣቸውን መመሪያ ለመቀበል ፈቃደኝነቱና ቅንነቱ ፈጽሞ የሌላቸው ሆነው መገኘታቸው አስቸኳይ መፍትሔ የሚሻ ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ችግር ሆኖ ተገኝቶአል፡፡

‹‹በይሉኝታ የራስ ዓሊ ቤት ተፈታ›› እንደ ተባለው ትዕግሥትና ደግነት በዚያም ላይ ይሉኝታ ተጨምሮበት ካልሆነ በቀር እነዚህን ወገኖች የምናስተናግድበት ቤትና የምንዳኝበት ሕግ ሳይኖረን ቀርቶ አይደለም፡፡ እውነቱን እንነጋገር ከተባለ በሃይማኖታችን ትውፊት ስመ እግዚአብሔርን ጠርቶ ጸበልን ቀምሶ የሚኖር የጽዋ ማኅበር ካልሆነ በቀር በቤተ ክርስቲያናችን ታሪክ ቤተ ክርስቲያንን አህሎ የተደራጀና ቤተ ክርስቲያን አከል የሆነ ገንዘብ ሰብሳቢ ማኅበር ታይቶም ተሰምቶም አይታወቅም፡፡ ስለሆነም በመልካም አስተዳደር፣ በሀብትና በንብረት አያያዝ፣ በመሪ ዕቅድ እየተመሩ ሥራ መሥራትን አስመልክቶ የተጀመሩ ሥራዎች አጠናክሮና አፋጥኖ ከዳር የማድረሱ ተግባር እንዳለሆኖ በተለይም በምእመናን ፍልሰትና በማኅበራት ጉዳይ ላይ በሕገ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሕጋዊና ዘላቂ መፍትሔ ማስቀመጡ ቤተ ክርስቲያንን የመታደግ ጉዳይ መሆኑን በአጽንዖት ሳንጠቁም አናልፍም፡፡

በመጨረሻም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ መላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን ግልጽ በሆነ ሁኔታ እያልን ያለነው፡-

1. የምእመናን ፍልሰት በአሁኑ ጊዜ እየተባባሰ ስለመጣ ሁላችንም ተባብረንና አስፈላጊውን ሥራ ሠርተን ፍልሰቱን እናስቁም፤

2. የቤተ ክርስቲያንን ሀብትና ንብረት በመጠበቅ መልካም አስተዳደርን እናስፍን፤

3. በቤተ ክርስቲያን ስም የሚሰበሰብ ነገር ግን ቤተ ክርስቲያን የማታውቀው፣ የማትቈጣጠረውና የማታዝበት ገንዘብና ሀብት ሊኖር አይገባም፤

4. በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ያልታቀፈና ለቤተ ክርስቲያን የማይታዘዝ ማኅበር በቤተ ክርስቲያን ስም ተደራጅቶ እንዲንቀሳቀስ ማድረግ ለቤተ ክርስቲያን ከሚሰጠው ጥቅም ይልቅ የሚያስከትለው ጉዳት ከባድ ስለሆነ፣ በሕግ ማስተካከል አለብን የሚሉትን ነው፡፡

ስለሆነም ሕዝበ ክርስቲያኑ ይህንን በግልጽ አውቆ የቤተ ክርስቲያኒቱን ወቅታዊ ችግር በመፍታት ረገድ የበኩሉን እገዛ እንዲያደርግ፣ እንደዚሁም በተሳሳተ መንገድ እየሄዱ ያሉትን ወገኖች በቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዐት ልትመሩ ይገባችኋል ብሎ እንዲመክራቸው፣ እነዚህ ወገኖች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆነው እንዲያገለግሉ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የበኩሉን ተጽዕኖ በመፍጠር ታሪካዊ ኀላፊነቱን እንዲወጣ አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ጉባኤያችንን ይባርክ፤ ይቀድስ፤አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc2014-10-22 20:51:542024-12-03 21:16:46ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: 33ኛው ዓመታዊ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከጥቅምት 5-8 ቀን 2007 ዓ/ም አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ Link to: 33ኛው ዓመታዊ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከጥቅምት 5-8 ቀን 2007 ዓ/ም አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ 33ኛው ዓመታዊ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ... Link to: ከጥቅምት 12 እስከ 26 ቀን 2007 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ Link to: ከጥቅምት 12 እስከ 26 ቀን 2007 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ ከጥቅምት 12 እስከ 26 ቀን 2007 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top