• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

የካቲት 16 ቀን የ2006 ዓ.ም ዐቢይ ጾምን አስመልክቶ ያስተላለፉት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በሙሉ፤

እግዚአብሔር አምላክ እንኳን ለሁለት ሺሕ ስድስት ዓመተ ምሕረት የጌታችን የአምላካችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መዋዕለ ጾም በሰላም አደረሳችሁ፡፡

‹‹ወእመሰ በምግባረ መንፈስ ቀተልክምዎ ለምግባረ ነፍስትክሙ ተሐይዉ ለዓለም፤ በመንፈሳዊ ሥራ ሥጋዊ ሥራችሁን ብትገድሉ ለዘለዓለሙ ትድናላችሁ›› (ሮሜ 8÷13)፡፡

ጾም ከጥንት ጀምሮ በዘመነ ብሉይም ሆነ በዘመነ ሐዲስ የተወደደ፣ የፈቃደ ሥጋ መቈጣጠሪያ፣ የፈቃደ ነፍስ ማበልጸጊያ መሣሪያ ነው፤ እነ ሙሴ፣ እነ ኤልያስና እነ ዳንኤል ከእግዚአብሔር ጋር በቀጥታ ይገናኙ የነበረ ራሳቸውን በጾም ለእግዚአብሔር በማስገዛት ነው፤ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾሞ፣ በሰይጣን የቀረበለትን ፈተና አሸንፎ፣ የጾምን ድል አድራጊነት በተግባርና በትምህርት አሳይቶናል፤(ማቴ.4÷1-11)

ቅዱሳን ሐዋርያትም እግዚአብሔር ሥራቸውን እንዲያቃናላቸው፣ ኀይለ መዊእ (የአሸናፊነት ኀይል) እንዲሰጣቸው በየጊዜው ይጾሙ ነበረ፤(የሐ.ሥ.10÷23) ሐዋርያዊት፣ ጥንታዊትና ህልውት በኵሉ የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም ከነቢያት፣ ከጌታችንና ከሐዋርያት በተማረችው ትምህርትና በተቀበለችው ትውፊት መሠረት ከእግዚአብሔር ጋር ለመገናኘት፣ ኀይለ አጋንንትን ድል ለማድረግ፣ ከእግዚአብሔር በረከትንና ረድኤትን ለማግኘት ጾምን ትጾማለች፡፡

ሰው በተፈጥሮው እርስ በእርስ የሚጋጩ ሁለት ፍላጎቶች በውስጡ እንዳሉ ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል፤ እነዚህ ፍላጎቶች ሥጋዊና መንፈሳዊ ተብለው የሚታወቁ ሲሆን፣ የሥጋ ፍላጎት ለነፍስ ፍላጎት፣ የነፍስ ፍላጎትም ለሥጋ ፍላጎት ተቃራኒ እንደሆነ በቅዱሳት መጻሕፍት ተብራርቶና ተገልጾ ተቀምጦአል፡፡ (ገላ.5÷16-18) ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን በተመለከተ ሲያስተምር ‹‹የሥጋ ፍላጎት ሞትን ያመጣል፤ የነፍስ ፍላጎት ግን ሰላምንና ሕይወትን ይሰጠናል››፤ ብሎአል፤ (ሮሜ.8÷6-8)፤ የጾም አስፈላጊነት የሚመነጨውም ከዚህ መሠረታዊ ትምህርት ነው፤ ሥጋ ኀይልና ሙቀት ሰጪ ምግቦችን አብዝቶ በተመገበ ቊጥር ኀይል ይሰማዋል፤በዚህ ጊዜ ለእግዚአብሔር መታዘዝን ይዘነጋል፣ ወንድሙን ለመበደል ይፈጥናል፣ ማመዛዘን አይችልም፤ ብዙ ስሕተትንም ይፈጽማል፤ በመጨረሻም ይሞታል ማለትም ከእግዚአብሔር ጋር አንድነትን ያጣል፤ ከመንፈሳዊ እይታ አንጻር ከእግዚአብሔር አንድነት መለየት እጅግ በጣም የከፋ ሞት ነው፡፡

በአንጻሩ ደግሞ ሰው ከምግብ በታቀበ ጊዜ ረጋ ብሎ ማሰብን፣ ማስተዋልን፣ ማመዛዘንን፣ ለእግዚአብሔር መታዘዝን፣ ራስን መግዛትን፣ ርኅራኄንና ቸርነትን፣ ለወንድም አዛኝነትን ገንዘብ ያደርጋል፤ በመጨረሻም ከእግዚአብሔር ጋር አንድነቱን ያጠናክራል፤ በዚህም የሞት አሸናፊ ሆኖ በእግዚአብሔር መንግሥት በዘለዓለማዊ ሕይወትና ክብር ተደስቶ ይኖራል፤ ከዚህ አኳያ ጾም ለመንፈሳዊ ሕይወት መጎልበት፣ ራስን በመግዛት ከእግዚአብሔር ጋር ልዩ ግንኙነትና አንድነት ለመፍጠር እጅግ አስፈላጊ ሆኖ ይገኛል፤ ጾማችን በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት አግኝቶ ሙሉ ዋጋ ሊያሰጠን የሚችለው ከፍቅር፣ ከምጽዋት፣ ከሰላም፣ ከጸሎትና ራስን ለእግዚአብሔር ከማስገዛት ጋር ሲሆን ነው።

በፍጹም ሐሳባችን፣ በሙሉ ኀይላችንና በፍጹም ልቡናችን ለእግዚአብሔር በምንገዛበት በዚህ ወቅት ካለን ሀብት ከፍለን፤ በየሰፈሩ የሚገኙ ጧሪ የሌላቸው አረጋውያንን፣ አሳዳጊ የሌላቸው ሕፃናትን፣ ሠርተው ራሳቸውን መርዳት ያልቻሉ የአካል ጒዳተኞችን በመርዳት ጾሙን ልንጾም ይገባል፡፡ ወርኀ ጾም በመንፈሳዊ ሕይወታችንም ሆነ በሥጋዊ ኑሮአችን ከምንም ጊዜ በበለጠ ግዙፍና ትላልቅ ሥራዎችን ሠርተን የምናጠናቅቅበት ጊዜ ሊሆን ይገባል፤ በተለይም በመንፈሳዊ ሕይወታችን ለእግዚአብሔር ያለንን ተገዢነት ለማረጋገጥ፤ በመንፈስና በጽድቅ ሆነን በየቀኑ አብዝተን የምንጾምበትና የምንሰግድበት መሆን አለበት፤ በሥጋዊ ኑሮአችንም ሥራ ከሚያስፈቱን ነገሮች ሁሉ ርቀን ቀኑን በሙሉ በሥራ ላይ የምንውልበት ሊሆን፤ ይገባል፤ በመሆኑም ሕዝበ ክርስቲያኑ በሀገራችን የተጀመረውን የአረንጓዴ ልማት ለማሳካት አፈርን የመገደብና መስኖን የማስፋፋት ሥራ አጠናክሮ እንዲሠራና ወርኀ ጾሙን በላቀ የሥራ ርብርብ እንዲያሳልፍ መልእክታችንን አደራ ጭምር እናስተላልፋለን፡፡

በመጨረሻም፡ እግዚአብሔር አምላካችን ወርኀ ጾሙን መልካም የንስሐ፣ የሰላም፣ የፍቅርና የሥራ ጊዜ አድርጎ በማስፈጸም ለጌታችን ለአምላካችንና ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ በሰላምና በጤና እንዲያደርሰን በጾምና በጸሎት እንትጋ በማለት መልእክታችንን በድጋሚ እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝባችንን ይባርክ ይቀድስ አሜን !!

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc2014-02-23 10:28:552024-12-05 10:30:01የካቲት 16 ቀን የ2006 ዓ.ም ዐቢይ ጾምን አስመልክቶ ያስተላለፉት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጥር 11 ቀን የ2006 ዓ.ም የጥምቀት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥር 11 ቀን የ2006 ዓ.ም የጥምቀት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥር 11 ቀን የ2006 ዓ.ም የጥምቀት በዓል ቃለ ምዕዳንና... Link to: ሚያዝያ 12 ቀን የ2006 ዓ.ም በዓለ ትንሣኤ Link to: ሚያዝያ 12 ቀን የ2006 ዓ.ም በዓለ ትንሣኤ ሚያዝያ 12 ቀን የ2006 ዓ.ም በዓለ ትንሣኤ
Scroll to top Scroll to top Scroll to top