• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ግቢ ውስጥ የተገነባውን የአብነት ትምህርት ቤት ባርከው ሥራ አስጀመሩ።

በቅዱስነታቸው ቡራኬ የተመረቀው ይህ የአብነት ትምህርት ቤት ክቡር ቢትወደድ ባሕሩ አብርሃም ከባለቤታቸው ክብርት ወ/ሮ ኢትዮጵያ ጥላሁን ጋር ከ133 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ አድርገው ያስገነቡት ነው።

በዚሁ የምርቃት መርሐ ግብር ከቅዱስ አባታችን በተጨማሪ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ሀድያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ሌሎችም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ሊቀ ሥልጣናት ቆሞስ አባ ሲራክ አድማሱ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስተዳዳሪ ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ካህናት አባቶች ፣ በአብነት ትምህርት ቤቱ ግንባታ ላይ የተሳተፉ መሐንዲሶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ቅዱስነታቸው በምርቃቱ ላይ ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ሲሰጡ “ቢትወደድ ባሕሩ አብርሃም የአብነት ትምህርት ቤት መገንባታቸው የቅድስት ቤተክርስቲያንን መሠረት የሚያጸና ሊቃውንትን ፣ ካህናትን ሊአስገኝ የሚችል ከሁሉም የበለጠ ለቅድስት ቤተክርስቲያን የሚጠቅም በጎ ተግባር ነው” ብለዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ኦርቶዶክሳዊያን ባለፀጋዎች ልክ እንደ ቢትወደድ ባሕሩ አብርሃም እግዚአብሔር ባርኮ የሰጣቸውን ሀብት ለትውልድ በሚጠቅም ዘመን ተሻጋሪ ሥራ ላይ አውለው በረከት እንዲያገኙም አባታዊ ጥሪ አቅርበዋል።

በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የተመረቀውን የአብነት ያስገነቡት ቢትወደድ ባሕሩ አብርሃም ባስተላለፉት መልእክት ደግሞ “በሕይወቴ የሚያስደስተኝ ቤተክርስቲያን ሲተከል የአብነት ትምህርት ቤትም አብሮ ሲሠራ ነው” ተብለዋል ።

ቢትወደድ ባሕሩ አክለውም በዚህ ታሪካዊ ካቴድራል ግቢ ውስጥ የአብነት ትምህርት ቤት ያስገነቡት “የአሁኑ ትውልድ ጥንታዊውን የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ትምህርት በተመቻቸ መልኩ እንዲማር” ስለሚፈልጉ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ዛሬ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ለመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የአብነት ትምህርት ቤት ሠርተው ያስረከቡት ቢትወደድ ባሕሩ አብርሃም ከባለቤታቸው ክብርት ወ/ሮ ኢትዮጵያ ጥላሁን ጋር ከዚህን ቀደም በልዩ ልዩ የአገራችን ክፍሎች በርካታ አብያተ ክርስቲያናትንና የአብነት ትምህርት ቤቶችን ማሳነጻቸው ይታወቃል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/p00001.jpg 299 448 eotcp https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg eotcp2026-05-30 14:18:482026-05-30 15:16:40ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ግቢ ውስጥ የተገነባውን የአብነት ትምህርት ቤት ባርከው ሥራ አስጀመሩ።
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በቫቲካን በቅድስት መንበር የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፉ ብፁዕ ካሪዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲን በቢሮአቸው ተቀብለው አነጋገሩ።
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ግቢ ውስጥ የተገነባውን የአብነት ትምህርት ቤት ባርከው ሥራ አስጀመሩ።
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ

Archives

  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤... Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በቫቲካን በቅድስት መንበር የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፉ ብፁዕ ካሪዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲን በቢሮአቸው ተቀብለው አነጋገሩ። Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በቫቲካን በቅድስት መንበር የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፉ ብፁዕ ካሪዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲን በቢሮአቸው ተቀብለው አነጋገሩ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top