መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ
ማቴ 3:1

ጥቅምት 13 ቀን 2012 ዓ.ም. በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በልዩ ልዩ ምክንያቶች ሃይማኖትን፣ ብሔርና ቋንቋን መሠረት ያደረገ የሰው መግደልና የአብያተ ክርስቲያናት አስምልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በፍጹም የሚያወግዘው መሆኑን የተሰጠ መግለጫ በቅዱስነታቸው ተላልፏል፡፡

«ተገሐሥ እምእኩይ ወግበር ሠናየ — ከክፉ ነገር ራቅ፤ ሰላምን ፈልጋት።»
(መዝ. 33፥12)

ጥቅምት 12 ቀን 2012 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

“ወይእዜኒ ረዐዩ ዘሀለዉ ኀቤክሙ መርዔቶ ለክርስቶስ፤ አሁንም በእናንተ ዘንድ ያሉትን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ (1ኛ ጴጥ. 2፥6)፡፡

 38ኛው የሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ ከጥቅምት 5-8 ቀን 2012 ዓ.ም. አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡

“አድኅነነ እግዚኦ አምላክነ፤ ወአስተጋብአነ እምአሕዛብ፣ ከመ ንግነይ ለስምከ ቅዱስ፣ ወከመ ንትመካሕ በስብሐቲከ” አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ አድነን፤ ቅዱስ ስምህን እናመሰግን ዘንድ፣ በምስጋናህም እንመካ ዘንድ ከአሕዛብ መካከል ሰብስበን።›› (መዝ. 105፥47)

መስከረም 16 ቀን 2012 ዓ.ም በመስቀል ደመራ በዓል ላይ የተላለፈ መልእክት

“በመስቀሉ ወበቃሉ አዕበዮሙ ለአበዊነ፤
በመስቀሉና በቃሉ አባቶቻችንን ከፍ ከፍ አደረጋቸው።”
(ቅዱስ ያሬድ)

መስከረም 1 ቀን 2012 ዓ.ም. የዘመን መለወጫ በዓልን ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

“አመ ርእሰ ሳብዕ ወርኅ ግበሩ መጥቅዐ፤ በሰባተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ዕረፍት፣ በመለከት ድምፅ መታሰቢያ የተቀደሰ ጉባኤ ይሁንላችሁ” (ዘሌ. 23፥24)፡፡

ጳጒሜን 2 ቀን 2011 ዓ.ም.የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ሊቀ አእላፍ በላይ መኮንን የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ለመክፈት ባዘጋጀው ቡድናዊ አሠራር መሠረት አሽቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ጠርቶ ለሦስት ቀናት ዝግ ጉባኤ አድርጎ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡

ጳጒሜን 2 ቀን 2011 ዓ.ም.

ሰኔ 21 ቀን 2011 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ ችግር አስመልክቶ ከሰኔ 21 እስከ ሐምሌ 4 ቀን 2011 ዓ.ም. ድረስ ለሁለት ሱባኤ ጸሎተ ምሕላ እንዲደረግ መታወጁን ቅዱስነታቸው በሐዋርያዊ መግለጫ አስታውቀዋል፡፡

ሐምሌ 4 ቀን 2011 ዓ.ም.

ከግንቦት 14 ቀን እስከ ሰኔ 3 ቀን 2011 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡

የሕዝብና ቤት ቈጠራው በትክክል ይካሄድ፣ ስለተመለሡልን ሕንጻዎች በማመስገን ቤተ ክርስቲያናችን ከመንፈሳዊ አገልግሎት በተጨማሪ በማኅበራዊ ዘርፍ ለሀገር እድገትና ለሕዝቦች ኑሮ መሻሻል፣ በተለይም ለሀገራዊ ሰላምና አንድነት በመቆም ድርሻዋን እንድትወጣ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል

ግንቦት 14 ቀን 2011 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

“ወናሁ ወሀብኩክሙ ሥልጣነ ትኪዱ ዲበ ዐቃርብት ወዲበ አራዊተ ምድር ወዲበ ኵሉ ኀይለ ጸላኢ ወአልቦ ዘይነክየክሙ እነሆ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ በጠላትም ኀይል ሁሉ ላይ ሥልጣንን ሰጥቻችኋለሁ የሚጐዳችሁም ምንም የለም” (ሉቃ 10፥19)፡፡

ሚያዝያ 20 ቀን 2011 በዓለ ትንሣኤ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

“ወለእግዚአብሔር አኰቴት ዘወሀበነ ንማዕ በእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፤
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።” (1ቆሮ. 15፡57)፡፡

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ዐበይት የሥራ ክንውኖችና አባታዊ መመሪያዎች

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በቅዱስ ፓትርያርክነት ሥልጣን ከተሠየሙበት ጊዜ አንሥቶ እስከ አሁን ድረስ እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ በቅዱስ ሲኖዶስ እያስወሰኑ ለቤተ ክርስቲያናችን በርካታ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች መቀላጠፍ ዐይነተኛ ጠቀሜታ ያላቸው መመሪያዎችን አስተላልፈዋል፡፡

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ

መድኀኔ ዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላካዊ የማዳን ሥራውን ወደ ዓለም እንዲያዳርሱ ዐሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርትን ከዐሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል መርጦ ለሦስት ዓመት ከአራት ወር ከዐሥር ቀን አምላካዊ ትምህርተ ወንጌልን አስተምሮአቸዋል፡፡ ከዋለበት እየዋሉ ካደረበት እያደሩ አምላካዊ ትምህርቱን ሰምተው፣ መለኮታዊ ገቢረ ተኣምሩን አይተው፣ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑን ተረድተዋል፡፡ (ዮሐ. 6) ካመኑ በኋላ “ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ፤ ያመነ የተጠመቀ ይድናል@ ያላመነ ግን ይፈረድበታል”፡፡ (ማር.16፥15-16) ብሎ አዘዛቸው፡፡ በክርስትና ትምህርት ይህ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ የሰጠው ወንጌልን ለዓለም ሁሉ የማስተማር (የመስበክ) ተልእኮ “ዐቢይ ተልእኮ” (great mission) ተብሎ ይጠራል፡፡

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት የተከበረው የጸሎተ ሐሙስ በዓል እንደተለመደው በጾም፣በጸሎት፣ በኅጽበተ እግር ሥነ ሥርዐትና በሥርዐተ ቅዳሴ ተከብሯል፡፡ሙሉ ሥነ ሥርዐቱ በቅዱስ ፓትርያርኩ የተመራ ሲሆን ቀኑ የትሕትና የፍቅር ስለሆነ ይህንን የጌታችን የአምላካችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትሕትና ተግባር ሁሌም ከልባችን ጽላት ላይ በመጻፍ ምእመናን የሕይወታቸው መርሕ እንዲያደርጉት አሳስበዋል፡፡

ያግኙን