• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

የካቲት 16 ቀን 2012 ዓ.ም የዐቢይ ፆም መግቢያ መልእክት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገር ውስጥና በተለያዩ የውጭ ሀገር ክፍለ ዓለማት የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት፣ እንዲሁም ኢትዮጵያውያን የሆናችሁ ወገኖቻችን በሙሉ፡፡ በጾምና በጸሎት፣ በሰላምና በፍቅር የሚቀርብለትን የምእመናን ተማኅፅኖ ተቀብሎ ምሕረትንና ይቅርታን ለሕዝቡ የሚያድል እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሁለት ዓመተ ምሕረት የጾመ ኢየሱስ ሱባዔ በሰላም አደረሳችሁ፡፡

“ቅረቡ ኀቤሁ ወያበርህ ለክሙ፤ ወኢይትኀፈር ገጽክሙ
ወደ እርሱ ቅረቡ፤ ያበራላችሁማል፣ ፊታችሁም አያፍርም።”
(መዝ. 34፥5)

አምላካችን እግዚአብሔር የምልአተ ዓለም የበላይ ጠባቂና አስተዳዳሪ፣ መጋቢና መሪ፣ ውሳኔ ሰጭና ተቈጣጣሪ ነው፤ እግዚአብሔር በምልአተ ዓለም ውስጥና ከዚያም በላይ በምልአትና በርቀት ያለ ነውና ሁሉንም ማድረግ የሚቻለውና የሚሳነው ነገር የሌለ የኀያላን ኀያል፣ የጥበበኞች ጥበብ፣ የልዑላን ልዑል ነው፡፡ የፍጡራን ችግሮች በሙሉ ሊቀረፉ የሚችሉት በእሱ ፈቃድና ጥበብ ብቻ ነው፤ እኛ ፍጡራን የእርሱ ፈቃድ ማስፈጸሚያ እንሆን እንደሆነ እንጂ በራሳችን ዕውቀትና ጒልበት ብቻ የምናከናውነው ሥራ፣ የምናርቀው መከራ የለም፤ ይህንን ማድረግ የሚያስችል ዐቅም ቢኖረን ኖሮ ዓለማችን ሁሌ በሥጋት ተወጥራ ለመኖር አትገደድም ነበር፡፡

እግዚአብሔር በዳኝነቱ ኰናኒ በርትዕ፣ ፈታሒ በጽድቅ ነውና በበደላችን ከመፍረድ ወደኋላ ስለማይል ኰናኒ በርትዕ ይባላል፤ ንስሓ ገብተን፣ በጾምና በጸሎት ልባችንን ሰብረን፣ ወደእርሱ ከተመለስን ደግሞ፣ ምሕረቱንና ይቅርታውን ለመስጠት ጊዜ የማይወስድ ነውና ፈታሒ በጽድቅ ይባላል፡፡ ‹‹እስከ ሺሕ ትውልድ ቸርነትን የሚጠብቅ፣ አበሳንና መተላለፍን፣ ኀጢአትንም ይቅር የሚል፣ በደለኛውን ግን ከቶ የማያነፃ ነው›› የሚለው፣ የእግዚአብሔር ቃልም ይህንን ያረጋግጣል፤ ይህም ማለት ንስሓ ገብቶ በጾምና በጸሎት ለሚቀርብ ይቅር የሚል፣ ንስሓ ሳይገባ በበደሉ ጸንቶ ለሚኖር ግን ይቅር የማይል እውነተኛ ዳኛ ነው ማለት ነው፡፡ እንግዲህ ችግርንና ጭንቀትን የማስወገድ ፍጹምና ወሳኝ ኀይል ያለው እግዚአብሔር ብቻ ከሆነ በዓለማችንም ሆነ በሀገራችን እንደዚሁም በየግላችን ከሚያጋጥሙን ፈተናዎች እንዲታደገን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ግዴታችን ይሆናል፤ ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ ደግሞ የተሰበረ ልብ ሊኖረን ይገባል፤ የተሰበረ ልብ ማለት በበደሉ እጅግ የተጸጸተና ዳግም ኀጢአትን ላለመፈጸም በቍርጥ የወሰነ ማለት ነው፤ ከዚህ አንጻር ጾም የኅሊና ጸጸትን ከፍ በማድረግ ለእግዚብሔር እንድንታዘዝ የሚያደርገን ፍቱን መሣሪያ ነው፤ ስለሆነም ወደ እግዚአብሔር ቀርበን ለመለመንና ለመሰማት፣ ወደ ንስሓም ለመገሥገሥ ጾምና ጸሎት አስፈላጊዎቻችን ናቸው ፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን፤

ጾም ከመጀመሪያው ሰው ከአዳም ጀምሮ የቀደምት አበው፣ የነቢያት፣ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስና የሐዋርያት፣ እንደዚሁም የሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ቀዋሚ ሕግ ነው፤ ውጤቱም ምሕረትና ይቅርታ፣ ሰላምና መዳን እንደሆነ በነነዌ የሆነውን ታሪክ ማስረጃችን ነው፡፡ ጾም የኀጢአትና የበደል አበጋዝ የሆነው ዲያብሎስን ድል ለማድረግም ዐቢይ መሣሪያ ነው፤ ዲያብሎስ በአዳም ያስለመደውን በመብል አሳስቶ የመጣል ስልት፣ ጌታችን በጾም ኀይል አሳፍሮና ድል አድርጎ እንደመለሰው ከቅዱስ ወንጌል እንማራለን፤ በዚህም ጾም ፈቃደ እግዚአብሔር በፈቃደ ዲያብሎስ ላይ የበላይነትን እንዲጐናጸፍ የሚያደርግ ረቂቅ ኀይል እንደሆነ እንገነዘባለን፤ እኛ ክርስቲያኖች ጾምን የምንጾመው ከዚህ በላይ በተጠቀሰው መሠረታዊ አስተምህሮ ነው፡፡

ጾም የሚያስገኘው መንፈሳዊ ኀይል ብዙ እንደሆነ ሁሉ፣ ሠራዊቱም ብዙ ነው፤ ጾም ሲባል ብዙ ጊዜ ወደ ሰዎች አእምሮ የሚመጣው የእንስሳት ውጤት ከሆኑ ምግቦች መከልከልና ሰዓታትን ጠብቆ መመገብ የሚለው ነው፤ ነገር ግን የጾም ዐላማ በንስሓ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ነውና ከምግብ መከልከል ብቻ ወደ እግዚአብሔር እንድንቀርብና መልስ እንድናገኝ የሚያስችለን አይደለም፤ ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ በፍጹም ሓሳባችን፣ በፍጹም ልባችን፣ በፍጹም ነፍሳችን ነውና በአካላችንና በመንፈሳችን ሁሉ ለእግዚአብሔር ሙሉ በሙሉ ለመታዘዝ ዝግጁ በመሆን ልንጾም ይገባል፡፡ በመሆኑም በጾም ወቅት ከጥላቻና ከዛቻ፣ ፍትሕን ከማጕደልና ሰውን ከመበደል፣ ከቂምና ከበቀል ርቀን፣ እጃችንም፣ እግራችንም፣ አፋችንም፣ ዓይናችንም፣ ጆሮአችንም፣ ውስጣችንም፣ ውጫችንም ሁሉ በመልካም ሥነ ምግባርና በመንፈሳዊ ሕይወት አሸብርቀን መጾም ይገባናል፤ በዚህ ወቅት መስማትና ማዳመጥ ያለብን እግዚአብሔርና እግዚአብሔርን ብቻ ነው፤ የእግዚአብሔር ድምፅ ፍቅርና ሰላም፣ አንድነትና ስምምነት፣ ዕርቅና ይቅርታ፣ ምሕረትና ቸርነት፣ ርኅራኄና ኀዘኔታ፣ ጸሎትና ምፅዋት፣ ፍትሕና እውነት፣ እኩልነትና ኅብረት ነው፡፡ እነዚህን በሥራ በመተርጐም እየጾምን ወደ እግዚአብሔር ከቀረብን የጨለመብንን ሁሉ ያበራልናል፤ በፊቱም ሳናፍር የፈለግነውን ሁሉ አግኝተን እንመለሳለን ፡፡

በመጨረሻም፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ ከገጠማት ሥጋትና ጭንቀት ለመገላገል በጾምና በጸሎት ወደ እግዚአብሔር በመቅረብ ከመማፀን የተሻለ አማራጭ ሊኖር አይችልምና ሕዝበ ክርስቲያኑ የተቸገሩትን በመርዳት፣ በጾም፣ በጸሎት፣ በሰቂለ ኅሊና፣ በተመሥጦ ልቡና፣ ጽሙድ እንደ በሬ፣ ቅኑት እንደ ገበሬ ሆኖ ስለ ሀገር ሰላም፣ ስለሕዝቦች አንድነትና እኩልነት መጠበቅ፣ ወደ እግዚአብሔር በምሕላ እንዲያመለክት በእግዚአብሔር ስም መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር ወርኀ ጾሙን በሰላም አስፈጽሞ ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም ያድርሰን፤ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ይቀድስ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32020-02-24 14:00:112025-01-28 14:01:17የካቲት 16 ቀን 2012 ዓ.ም የዐቢይ ፆም መግቢያ መልእክት
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የካቲት 11 ቀን 2012 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የእነ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን ሥልጣነ ክህነት በውሳኔ ማገዱን ቅዱስነታቸው እንደሚከተለው ገልጸዋል፡፡ Link to: የካቲት 11 ቀን 2012 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የእነ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን ሥልጣነ ክህነት በውሳኔ ማገዱን ቅዱስነታቸው እንደሚከተለው ገልጸዋል፡፡ የካቲት 11 ቀን 2012 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ... Link to: መጋቢት 13 ቀን 2012 ዓ.ም የደብረ ዘይት በዓል መልእክት የሚከተለው ነው Link to: መጋቢት 13 ቀን 2012 ዓ.ም የደብረ ዘይት በዓል መልእክት የሚከተለው ነው መጋቢት 13 ቀን 2012 ዓ.ም የደብረ ዘይት በዓል መልእክት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top