• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ጥቅምት 12 ቀን 2009 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፡ ከየሀገረ ስብከታችን አሰባስቦና በዚህ ቅዱስ ስፍራ አገናኝቶ ስለአጠቃላይ መንፈሳዊ ተልእኮአችን ለመወያየት ያገናኘን እግዚአብሔር አምላካችንን እናመሰግነዋለን፡፡

“ኦ አባ ቅዱስ ዕቀቦሙ በስምከ ለእለ ወሀብከኒ ከመይኩኑ አሐደ ብነ ከማነ፤ ቅዱስ አባት ሆይ እነዚህን የሰጠኸኝን እንደ እኛ አንድ እንዲሆኑ በስምህ ጠብቃቸው” (ዮሐ17፡11)፡፡

በቃለ እግዚአብሔርም ሆነ በገሃዳዊው ዓለም ተጨባጭ አኗኗር እንደሚታየው የፍጡራን አንድነት ተፈጥሮኣዊ ጸጋ ከመሆን አልፎ አስገዳጅ የህልውና ዋስትናም እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል፡፡ የአንድነት አስፈላጊነት በተመሳሳይ ዘርዐ ፍጡራን ብቻ የሚወሰንም አይደለም፤ በምንኖርባት ዓለም የሚገኙ የሚንቀሳቀሱና የማይንቀሳቀሱ ፍጡራን በአጠቃላይ፣ አንድነት ኖሮአቸው እርስ በርስ የማይመጋገቡ ከሆነ ህልውና ጣዕም አይኖረውም ብቻ ሳይሆን ጭራሽኑ መኖር እንደማይችሉ ግልጽ ነው፡፡

እግዚአብሔር በከሃሊነቱ እርስ በርስ አቆራኝቶ አስተሳስሮና ተመጋጋቢ አድርጎ የፈጠራቸውን ፍጡራን በሰው ሠራሽ ምክንያት ለማለያየት መጣር፣ ሙከራ ከመሆን አልፎ ዘላቂ የሆነ ተቀባይነት ሊኖረው አይችልም፤ ምክንያቱም ፍጡራን ሁሉ ማኅበራውያንም አሐዳውያንም ሆነው ሊኖሩ በአምላክ ጸጋ ተፈጥረዋልና ነው፤ ዛሬ ዓለም በአጠቃላይ በኢኮኖሚና በማኅበራዊ ሕይወት እንደ አንድ መንደር እየሆነች የመጣችው በራስዋ ጥበብ ሳይሆን እግዚአብሔር ጥንቱም ማኅበራዊ ሆና እንድትኖር አድርጎ ስለፈጠራት ነው፡፡

ጌታችን፣ አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ወደዚህ ዓለም የመጣው በፍጡራን መካከል ጠንካራ ኅብረትና አንድነት እንዲኖር ለማድረግ ነው፤ ጌታችን በትምህርትም በተግባርም ያረጋገጠውም ይኸው ነው፡፡ ጌታችን ለፍጡራን በአጠቃላይ፣ በተለይም ለሰው ልጅ ያስተማረው የአንድነት ትምህርት ከራሱና ከባሕርይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብ ጋር ካለው መለኮታዊና ባሕርያዊ አንድነት ጋር በማነጻጸር መሆኑንም የአንድነት አስፈላጊነት ምን ያህል ትልቅ ስፍራ እንዳለው የሚያሳይ ነው፡፡

የጌታችን ትልቁ ጸሎትና ትምህርት የሰዎች አንድ መሆን እንደሆነ ከቅዱስ ወንጌል ተምረናል፣ አውቀናልም፤ በመሆኑም ክርስቶሳዊ፣ ሐዋርያዊና ዐቢይ የሆነው ይህ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ፣ የጌታችንን ትምህርትና ትእዛዝ የመጠበቅና የማስጠበቅ የመፈጸምና የማስፈጸም ኀላፊነት እንዳለበት መዘንጋት የለብንም፡፡

እኛ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሕዝብን አንድነት ለመጠበቅ ሕዝብን የሚያስማማና የሚያግባባ ትምህርት ማስተማር ይገባናል፣ ማስተማርም ያለብን ምንም ምን ያልተቀላቀለበት ንጹሕ የእግዚአብሔር ቃል ሊሆን ይገባል፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ሁሉንም ያስማማል ሁሉንም ያግባባል በመስማማት ላይ የተመሠረተ አንድነትም ፍሬ ሰላምን ያፈራል፡፡

እኛ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሰላም ሐዋርያት ሆነን በጌታችን ተሹመናል፤ ለሕዝቡ ሁሉ የእግዚአብሔርን ሰላም እንድናደርስም “ሰላማችሁ ይድረስለት” ተብለን ሰላመ እግዚአብሔር በእኛ በኩል ለሕዝቡ ተልኮአል፤ አሁን ጥያቄው የሰላም ተልእኮውን ለሕዝቡ እንድናደርስ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠንን አደራ በሚገባ እያደረስን ነው ወይ? የሚለው ነው፤ መልሱ አጭርና ግልጽ፣ እየታየም ያለ ይመስለናል፡፡

እኛ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በዚህ ዓለም ንጹሕ የሆነውን የእግዚአብሔር ቃል እንዳናስተምርና ሕዝቡን አስማምተን አንድ እንዳናደርግ የሚከለክለን እንደሌለ እናውቃለን፣ ነገር ግን ማስተማር የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እያለ በሚገባ ባለማስተማራችን ሕዝቡ ግራ ከተጋባ የጎደለ ነገር አለ ማለት ነው፤ እርግጥ ነው ይህን ስንል ሥራ አልተሠራም ትምህርትም አልተሰጠም ማለታችን አይደለም፤ነገር ግን እኛ ማየት ያለብን ጌታችን “ወገቢረክሙ ኵሎ በሉ አግብርት ፅሩዓን ንሕነ” ብሎ ያስተማረውን ነው፡፡

ዛሬ ሌሎች፣ ከእኛ ጉድለት አለ፤ እኛ አስተካክለን መሥራት የሚገባንን አልሠራንም እያሉ ለበለጠ ሥራ ሲዘጋጁ፣ የቃሉ መልእክተኞች የሆን እኛ ይህንን እውነተኛ የጌታችን ቃል ልናልፈው አይገባም፣ እየሆነ ያለው ሁኔታም ሲታይ ሕዝቡ የስምምነት፣ የአንድነት፣ የሰላምና የፍቅር ሕዝብ እንዲሆን ለማድረግ የሚቀረን ሥራ እንዳለ ያመለክታል፡፡ ሕዝቡ የእግዚአብሔር ማእደ ሰላም ከሆነች ቤተ ክርስቲያኑ የሰላምን ማእድ መቋደስና ማጣጣም እንዲችል ያለማቋረጥ ስለ ሰላምና ስለፍቅር ጠንክረን ማስተማርና መሥራት ይገባናል፡፡

በተለይም በአሁኑ ጊዜ በሀገራችን የተከሠቱ ግጭቶችና ሁከቶች ለዘላለም ተፈቃቅረውና ተዋደው ለዘመናት በአንድነት የኖሩትን የሀገራችን ሕዝቦች እርስ በርስ እንዲቃቃሩ ከማድረጉም ባሻገር የሕይወት ጥፋትና የንብረት ውድመት አስከትሎአል፣ የልማት አውታሮችን ጎድቶአል፤ ብዙ ዜጎችንን ያለሥራ አስቀርቷል በሕዝቦች መካከል የኅሊና ስብራት ፈጥሮአል፤ ይህ ለቤተ ክርስቲያናችንም ሆነ ለሀገራችን አሳዛኝ ክሥተት ነው፡፡

ቤተ ክርስቲያናችን የሕዝብ ሁሉ እናት ናት፤ እናት ከሁሉ በፊት ለልጇ ደራሽ እንደመሆኗ መጠን ቤተ ክርስቲያናችንም ችግሩ ከተከሠተበት ጊዜ አንሥቶ ኀዘኗንና የሰላም ጥሪዋና በተደጋጋሚ ስትገልጽ ቆይታለች፡፡ ይሁንና አሁንም የተከሠተው የሰላም መደፍረስና የኅሊና ስብራት ቀላል ስላልሆነ ሰላሙ አስተማማኝ እስኪሆንና የኅሊና ስብራቱም ተጠግኖ እስኪሽር ድረስ በሰላም መጠናከር ዙርያ መጠነ ሰፊ የሆነ ሥራ መሥራት ይኖርብናል፡፡

ቤተ ክርስቲያናችን የሁሉም እናት ነች ስንል የኢትዮጵያ ሕዝቦችም በሙሉ ልጆችዋ ናቸው ማለታችን ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ወደዚህም ወደዚያም ሳትል ማእከላዊና ገለልተኛ ሆና የሰላም መልእክቷን ብቻ ለሁሉም ማድረስ ይገባታል፡፡

ቤተ ክርስቲያናችን ዘላቂና ብዙኃኑን የሚጠቅም የሰላም ህልውናን ለማረጋገጥ በሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ ተሳትፎዋን በማሳደግ ለሕዝብና ለሀገር ደኅንነት መሥራት ይኖርባታል፡፡ በተለይም ዘርን በመለየት የሀገርን አንድነት በመፈታተንና በሃይማኖት አመክንዮ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ሕዝባችንን ሀገራችንንና ሃይኖታችንን በእጅጉ የሚጎዱ ስለሆኑ ሕዝቡ እንዲጠነቀቅባቸውና በአርቆ አስተዋይነት እንዲመለከታቸው በልዩ ትኵረት ማስተማር ይኖርብናል፡፡

ሕዝቦቻችን በተለይም ወጣት ልጆቻችን ለአደጋ እየተጋለጡበት ያለው ክፍተት የሥራ አጥነት ችግር እንደሆነ እየሰማን ነው፤ ሁሉም በልቶ ካደረ ችግሩ ሊቀንስ እንደሚችል ጥርጥር የለንም፡፡ ሆኖም የዚህ ቊልፍ መፍትሔ ልማትን በማስፋፋት ዕድገትን ማምጣት ነው፡፡ ዕድገቱን ሊያመጣው የሚችል ደግሞ እኛ እየመራነውና እያስተማርነው ያለው ሕዝብ ነው፡፡ ስለሆነም ሕዝቡ ዐቅሙን ሁሉ አስተባብሮ ወደ ልማት እንዲሠማራ ያለ መታከት ማስተማር ያለብን እኛው ብፁዓን ሊቃ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ካህናት ሰባክያነ ወንጌል ነን፤ ነገር ግን አስተማሪዎች ብቻ ሳንሆን ሠርተን የምናሳይም መሆን ስላለብን ቤተ ክርስቲያናችን በሁሉም አቅጣጫ ልማትን በማስፋፋትና ለወጣቱ ትውልድ የሥራ ዕድልን በመፍጠር እናትነትዋን በተጨባጭ ማሳየት አለባት፤

ስለሆነም በዚህ ቅዱስ ዓመታዊ ጉባኤያችን በሰላም መጠናከርና መጠበቅ ዙርያ፣ በልማት ሥራ መስፋፋትና በስብከተ ወንጌል መጠናከር ላይ ሰፊና ጥልቅ ውይይት በማድረግ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሕዝባችን እንደዚሁም ለሀገራችን በአጠቃላይ የሚጠቅሙ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ጉባኤውን እንድናጠናቅቅ በማሳሰብ፣ ለስኬቱም ያለንን ልባዊ ምኞትና ጸሎት በመግለጽ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በይፋ መከፈቱን እናበስራለን፡፡

እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32016-10-22 08:53:162024-12-07 08:55:58ጥቅምት 12 ቀን 2009 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: በ35ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ ጉባኤ ጥቅምት 7 ቀን 2009 ዓ.ም. አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ Link to: በ35ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ ጉባኤ ጥቅምት 7 ቀን 2009 ዓ.ም. አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ በ35ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ... Link to: ጥቅምት 11 ቀን እስከ 16 ቀን 2009 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ Link to: ጥቅምት 11 ቀን እስከ 16 ቀን 2009 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ ጥቅምት 11 ቀን እስከ 16 ቀን 2009 ዓ.ም የተካሄደው...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top