• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

በ35ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ ጉባኤ ጥቅምት 7 ቀን 2009 ዓ.ም. አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፤ ክቡራን የየመምሪያውና የየድርጅቱ ኀላፊዎች፣ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ከሚገኙ አህጉረ ስብከት የመጣችሁ ሥራ አስኪያጆችና ተወካዮች፣ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ተወካዮች፣ በአጠቃላይ በዚህ ዓመታዊና ዓለም አቀፋዊ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የተገኛችሁ ተሳታፊዎች በሙሉ፤

የምሕረት አባትና የሰላም ባለቤት የሆነው እግዚአብሔር አምላካችን ለዚህ ዓመታዊ የቤተ ክርስቲያናችን ዐቢይ ጉባኤ ስላደረሰን በቅድሚያ ክብርና ምስጋና ለእርሱ እናቀርባለን፡፡ እናንተንም እንኳን አደረሳችሁ እንኳንም በደኅና መጣችሁ እንላለን፡፡

“እንዘ አልብነ ኵሉ ብነ
አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የኛ ነው፤”
(2ቆሮ. 6፥10)፡፡

የሃይማኖት ጉዞ ሁሉ የመንፈስ ጒዞ ነውና በመንፈስ ጀምሮ በመንፈስ የሚጠናቀቅ እንጂ እንደገና ተመልሶ ወደ ግዙፉና ዓለማዊው ነገር የሚዘፈቅ አይደለም፤ እንደዚህ የሚሞከር ከሆነም ዐላማውን ስቶ ይወድቃል እንጂ ውጤታማ መሆን ፈጽሞ አይችልም፡፡

የሃይማኖት ሥራ በዋነኛነት የሚከናወነው በካህናት እንደሆነ ለሁሉም ግልጽ ነው፤ ካህናትም በትምህርተ ሃይማኖት ጸንተው፣ በኀይለ መንፈስ ቅዱስ ጎልብተው ዓለምንና በውስጡ ያለውን እየተዋጉ በማሸነፍ በድል አድራጊነት ወደፊት እንዲገሠግሡ እንጂ እንደገና በፍትወታት እኩያት ተሸንፈው ወደ ዓለማዊው አስተሳሰብና አኗኗር እንዲቀላቀሉ አልተፈቀደም፤ ካህናት የቆሙበት ስፍራና የተሸከሙት ኀላፊነት መለኮታዊ መንፈሳዊና ዘላለማዊ ነውና፤ ይሁን እንጂ ካህናት የመንፈስ ተቃራኒ የሆነውን አካለ ሥጋ የለበሱ በመሆናቸው ለሥጋዊ ኑሮአቸው የሚያስፈልግ ሁሉ በምእመናን እንዲሟላላቸው በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን በእግዚአብሔር ታዞአል፡፡

ካህናት እንደ ሐዲስ ኪዳኑ ሁሉ በብሉይ ኪዳንም በደብተራ ኦሪትና በዙርያው በነበረው የግብረ ክህነት አገልግሎት ሌት ተቀን ፅሙድ እንደ በሬ ቅኑት እንደ ገበሬ ሆነው በትጋት መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን ያከናውኑ እንደነበር እናውቃለን፡፡ ይሁንና ለኑሮአቸው የሚያስፈልገውን በተመለከተ የተፈቀደላቸው ቢኖር የዓለም የሆነውን ርስተ መሬት ሳይሆን ርስታቸው ራሱ እግዚአብሔር እንደሆነ ቅዱስ መጽሐፍ ያረጋግጣል ፤ ይህንንም አስመልክቶ ቅዱስ መጽሐፍ እንደዚህ ይላል “እግዚአብሔር አሮንን አለው፡- በምድራቸው ርስት በመካከላቸውም ድርሻ አይሆንልህም፤ በእስራኤል ልጆች መካከል ድርሻህና ርስትህ እኔ ነኝ”፤ (ዘኍ. 18፥20)፡፡ ይህም ማለት የካህናት ሥጋዊ ኑሮ በርስተ መሬት ላይ ሳይሆን በሃይማኖተ ምእመናን ላይ በተመሠረተ ቃለ እግዚአብሔር ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በሌላ አባባል፡- እግዚአብሔር ለካህናት የፈቀደው ርስት መሬታዊ ሳይሆን ዐሥራቱ፣ ቀዳምያቱና በኵራቱ ከምእመናን በነቂስ እየተከፈለ ለካህናት መተዳደሪያ ይሆን ዘንድ ለቤተ እግዚአብሔር እንዲሰጥ አድርጎአል ማለት ነው፤ (ዘፀ. 13፥2፣ ዘኍ. 18፥20-24፣ ዘሌ. 23፥9-14)፡፡ በዘመነ ሐዲስም ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያንኑ የኦሪቱን ዐስበ ካህን በማጽናት “ይደልዎ ዓስቡ ለዘይትቀነይ፤ ለሠራተኛ ደመወዙ ይገባዋል” ብሎአል (ማቴ.10፥10)፡፡

ከጥንት ጀምሮ ካህናተ እግዚአብሔር ይህ ነው ተብሎ የሚነገርና ግዙፍ የሆነ ምድራዊ ሀብት እንደሌላቸው ከላይ በተገለጸው ቃለ እግዚአብሔር ዋቢነት ማወቅ ይቻላል፤ ይሁን እንጂ ካህናት ኀላፊና ጠፊ የሆነው ምድራዊ ሀብት አይኑራቸው እንጂ የማያልፍና ተቈጥሮ የማያልቅ መለኮታዊ ሀብት በምድር ሳይቀር እንዳላቸው በቅዱሳት መጻሕፍት አስተምህሮም ሆነ በተግባር ታይቶአል ፡፡ ከዚህም የተነሣ ነው “ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው” ተብሎ በቅዱስ መጽሐፍ የተነገረው፤ነገሩም እውነት ነው ፤አንድ ካህን ብዙ ገንዘብ ወይም ሌላ ሀብት ላይኖረው ይችላል ፤ ነገር ግን በብዙ የሚቀጠሩ ምእመናን አሉት፡፡

ከዚህ አኳያ ካህን ምንም የሌለው ቢመስልም አያያዙን ካወቀበት ብዙ ሀብት ያለው ነው ብንል ፍጹም እውነት እንጂ ሽንገላ ሊሆን አይችልም፤ ሁላችንም ከምር ማወቅና መቀበል ያለ ብን ዐቢይ ጉዳይ ሀብት ማለት የገንዘብና የእንስሳት ብዛት ወይም የመሬት ይዞታ ስፋት ሳይሆን የሰው ብዛት መሆኑን ነው ፤ምክንያቱም የሰው ሀብት ካለ ሌላው ሁሉ ከሰው ዘንድ ይገኛልና ነው፤ ለእኛም ለካህናት ትልቁና ቋሚው ሀብታችን የሰው ሀብት ነውና አንዳች የሀብት ወረት የሌለን ስንሆን እንደ እግዚአብሔር ቃል ብዙ የሰው ሀብት አለን፡፡

ከዚህ አንጻር የቤተ ክርስቲያን ቀዋሚ ሀብቶች ምእመናን በመሆናቸው በየጊዜው ብዙ ችግሮች ሲያጋጥሙአት በምእመናን ድጋፍ ሁሉንም ስትወጣው ቆይታለች ፤የሩቁን ትተን ከዛሬ አርባ ዓመታት በፊት የሆነውን እንኳ ብንመለከት የነበራት የመሬት ሀብት ሁሉ በጊዜው በነበረው መንግሥት ሲወረስ የማይነጥፉና ቀዋሚ ሀብቶች ሆነው የደረሱላት ምእመናን ብቻ ነበሩ፡፡ በወቅቱ የቤተ ክርስቲያን ቀዋሚና የማይነጥፍ ሀብት ምእመናን ብቻ መሆናቸውን የተረዱት ቀደምት ቅዱሳን አበው በተለይም ሁለተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ምእመናንን በቃለ ዐዋዲ አደራጅተው ተገቢውን አስተዋፅኦ እንዲከፍሉ በማድረጋቸው በአሁኑ ጊዜ ከሞላ ጎደል ቤተ ክርስቲያናችን ተልእኮዋ በአግባቡ እንድትወጣ፣ የካህናት ኑሮም እንዲሻሻል ለማድረግ ተችሎአል፡፡

ይሁን እንጂ ጌታችን “ማእረሩ ብዙኅ ውእቱ ወገባሩሰ ኅዳጥ ውእቱ፤ አዝመራው ወይም መከሩ ብዙ ነው፤ ሠራተኛው ግን ጥቂት ነው” (ማቴ 9፡37) እንዳለው ዛሬም አዝመራው ብዙ ሆኖ ሳለ ሠራተኛው ጥቂት በመሆኑ ቀላል የማይባል ክፍተት ይስተዋላል፤ ይህም ማለት የሰው ኀይል እጥረት ባይኖር እንኳ ከአስተሳሰብና አሠራር ክፍተት የተነሣ አዝመራው በሚገባ ሳይያዝና ሳይጠበቅ እየቀረ ሌሎች ወፎች እየለቃቀሙት እንደሆነ በግልጽ ይታያል፡፡ ይህ ባይሆን ኖሮ ከኃምሳ ሚሊየን ያላነሱ ምእመናን ያሏት ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ በመቶ ሚሊዮን ሳይሆን በቢሊየኖች የሚቈጠር የገንዘብ ሀብት አሰባስባ ትላልቅ መንፈሳዊ ተቅዋማትን ትገነባ ነበር፤ በዚህም ሀብትዋ ተጠቅማ አረጋውያንንና አሳዳጊ አልባ ሕፃናትን፣ በየማእከሉ ሰብስባ በሚገባ ትረዳ ነበር፣ የትምህርትና የጤና ተቅማዋት የመሳሰሉትን ማኅበራዊና መንፈሳዊ ተቅዋማትንም በብዛት ከፍታ ለሕዝቡ ችግር መቃለል ፈጥኖ ደራሽ መሆን ትችል ነበር፡፡

ዛሬም ጊዜው እየነጋ እንጂ እየመሸ አይደለምና አሁንም ከሁሉ በፊት ሀብታችን ያለበትን አካባቢ በውል ማወቅ ይኖርብናል ሀብታችን ያለው በምእመናን ልቡና ውስጥ ነው፡፡ እሱን በእግዚአብሔር ቃል አለስልሰን፤ በሥነ ምግባር ኰትኵተን ለመልካም ፍሬና ለጥሩ ምርት ማብቃት አለብን፤ ከአያያዝና ከትምህርት ጒድለት አንድ ምእመን ከበረታችን በተወሰደ ቍጥር ሀብታችን እየቀነሰ መሆኑን በውል እንገንዘብ ፤ምእመናን እስከ በዙና እስከተጠበቁ ድረስ ካህናት ሀብታሞች ነን ፤ ምእመናን እየቀነሱ በሄዱ ቊጥር ግን መደኽየታችን የማይቀር ነው፡፡ ስለዚህ እኛ ካህናት ሁሌም መጨነቅ ያለብን ስለ ሀብት ድልብ ሳይሆን ስለምእመናን ድልብ ነው፤ ምእመናን ካሉ ሀብቱ አለና፤ ከኃምሳ ሚሊዮን በላይ ምእመናን ካሉንና በእነርሱ ላይ ተገቢ ጥበቃና አገልግሎት ካበረከትን የሚጎድልብን አንዳች ነገር አይኖርም፤ የሰበካ ጉባኤ ዐቢይ ተልእኮም ይኸው ነው፤ እስካሁን በሚታየው ተጨባጭ እውነታ የሰበካ ጉባኤ ዐላማ እኛ ካህናት ሀብታሞች መሆናችንን ያረጋገጠ ወንጌላዊ መሣሪያ እንደ ሆነ ከቶውኑ ልንዘነጋ አይገባም፡፡

ሰበካ ጉባኤ ትልቅና አስተማማኝ የሀብት ምንጭ እንደሆነ ተረጋግጦ ባለበት ሁኔታ እድገቱ አዝጋሚ ሆኖ መታየቱ ችግሩ የእኛ እንጂ የመሠረተ ዐላማው አለመሆኑን በሚገባ መታወቅ ይኖርበታል፡፡ ዛሬም፣ ነገም፣ ቤተ ክርስቲያናችንን ወደ ላቀ መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ የእድገት ደረጃ ለማሸጋገር ብቸኛውና ዋነኛው ቊልፍ ሰበካ ጉባኤ መሆኑን ሁላችንም ልናሠምርበት ይገባል፤ ስለሆነም እኛ ካህናት ሌት ተቀን በመሥራት፤ ምእመናንን እንደ እግዚአብሔር ቃል በመጠበቅና በመንከባከብ እንደዚሁም የሚጠበቅብንን መልካም ሥነ ምግባር ሁሉ ለምእመናን በማሳየት የቤተ ክርስቲያናችንን እድገትና ሉዓላዊ ክብር እስከ መጨረሻው ማስከበር ይጠበቅብናል፤

የካህናት መደበኛ ሥራ ምእመናንን ከማንኛውም ጒዳት መጠበቅ እንደሆነ የማይካድ ነው፤ የምእመናን ጥበቃም የተሟላ እንዲሆን በሀገር ዐቀፍ ደረጃ ከዚያም አልፎ በዓለም ዐቀፍ ደረጃ የተሟላ ሰላም መኖር የግድ ይላል፤ የመጀመሪያው ጥበቃም ማተኰር ያለበት በሰላም መረጋገጥ ላይ ነው፤ ምክንያቱም ሰላም ከሌለ ምእመናን የሚጠመቁበትና የሚቈርቡበት ቤተ ክርስቲያንም አደጋ ላይ ይወድቃል፤ በሰላም ወጥቶ ቤተ ክርስቲያን ደርሶና ከእግዚአብሔር ጋር ተገናኝቶ መመለስም ይቆማል፤ በዚህ ሁሉ ሃይማኖቱ ራሱ አደጋ ላይ ይወድቃል፤ ባለፉት ወራት በሀገራችን የተከሠተው የሰላም መደፍረስ አደጋ ያሳየን ነገር ቢኖር ይኸው የምእመናን ጒዳት ነው፡፡ በተለይም ዘርንና ሃይማኖትን ለይቶ የሀገርን አንድነት ለመናድ የሚደረገው ሙከራ ጎጅነቱ ወደር የማይገኝለት ነው፡፡ የኦሮሞ የኢሬቻ በዓል ላይ የደረሰው የሰው ዕልቂትም በኢትዮጵያውያን አእምሮ ውስጥ ቊስል አሳልፎ አልፏል፡፡ በዚህም ምክንያት ምእመናን ከተጎዱ ቤተ ክርስቲያን በቀጥታ ትጎዳለች፤ የሀገር ሰላም ከደፈረሰ ጒዞው ሁሉ ወደፊት መሆኑ ቀርቶ የኋልዮሽ ይሆናል፡፡ ታዲያ የኛ መምህርነትና አባትነት ለዚህ ጊዜ ያልሆነ ለመቼ ሊሆን ነው? እኛ አስተምረነው፣ መክረነው ታረቅ ብለነው የማይሰማን ሰው በዚህች ሀገር ይኖራል ብለን አናስብም፡፡

ስለሆነም ከላይ ጀምሮ እስከ ታች ያሉ የቤተ ክርስቲያናችን ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት መምህራን ሊቃውንትና ካህናት በሙሉ የነበረን የሰላም ሀብት ልማታችንና እድገታችን በማይዋጥላቸው ባዕዳንና በሌሎች አካላት ሳይነጠቅ በነበረው ዐይነት ተጠብቆ እንዲቀጥል ለማድረግ ዙርያ መለስ ርብርብ ማድረግ ይገባናል፡፡ ሕዝባችን ሰላምን፣ እድገትን፣ አንድነትን፣ ልማትን፣ እኩልነትን፣ ፍትሓዊነትን፣ መልካም አስተዳደርን ብቻ እንደሚፈልግ እየነገረን ነው፡፡ ሕዝቡ ይህ ጥያቄ እንዲመለስለትና እውን እንዲሆንለት በመንግሥትና በሕዝቡ መካከል አገናኝ ድልድይ ሆነን መሥራት ይኖርብናል፤ ከእግዚአብሔር የተቀበልነው አደራና ተልእኮም ይኸው ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ በእሬቻ በዓልና በሌሎችም አካባቢዎች በተፈጠረው ሁከትና ግርግር ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችን ሁሉ እግዚአብሔር በመንግሥቱ እንዲቀበልልን፣ ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናትን እንዲሰጥልን፣ወደፊትም ሕዝባችንን ከመሰል አደጋ እንዲጠብቅልን፣ ጸሎታችንን ወደ እግዚአብሔር እናቀርባለን፡፡

በመጨረሻም፡ ይህ ዐቢይ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን ዐበይት ጉዳዮችና በሀገራዊ ሰላም መጠበቅ ዙሪያ በሰፊው ተወያይቶ የበኩሉን ለማድረግ ቃል በመግባት ስብሰባውን እንዲያጠናቅቅ እያሳሰብን ሠላሳ አምስተኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው ዕለት መከፈቱን እናበሥራለን፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32016-10-17 14:44:582025-01-28 14:46:08በ35ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ ጉባኤ ጥቅምት 7 ቀን 2009 ዓ.ም. አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: መስከረም 16 ቀን የ2009 ዓ.ም. በበዓለ መስቀል ላይ በአደባባይ የተሰጠ መልእክት Link to: መስከረም 16 ቀን የ2009 ዓ.ም. በበዓለ መስቀል ላይ በአደባባይ የተሰጠ መልእክት መስከረም 16 ቀን የ2009 ዓ.ም. በበዓለ መስቀል ላይ... Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2009 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2009 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥቅምት 12 ቀን 2009 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top