• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

የካቲት 25 ቀን 2011 ዓ.ም. የዐቢይ ጾም መግቢያ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ወምእመናት በሙሉ፣ የምሕረት ጌታ የብርሃን አባት የሆነው እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ መዋዕለ ጾም በሰላም አደረሳችሁ፡፡

“እስመ ኅሊናሁ ለነፍስትነ ፀሩ ለእግዚአብሔር ውእቱ
የሥጋችን አስተሳሰብ የእግዚአብሔር ጠላት ነው።”
(ሮሜ 8፥7)

እኛ ሰዎች ከሁለት ነገሮች የተገኘን ውሕድ ፍጥረቶች መሆናችን ከእግዚአብሔር ቃል በተጨማሪ በየዕለቱ የምናሳየው እርስ በርሱ የተቃረነ ድርጊት ተጨባጭ ማስረጃ ነው፤ ከዚህ አኳያ ሰው ሁሉ ከአንድ ምንጭ የተገኘ በመሆኑ ከመንፈስና ከሥጋ የተገነባ ድንቅ ፍጡር ነው፤ ሥጋና መንፈስ በሰው ዘንድ በተዋሕዶ ይኑሩ እንጂ ፍጹም ስምምነት ያላቸው ነገሮች ግን አይደሉም፤ ይልቁንም በመካከላቸው ከባድ ተቃርኖ እንዳለ “እስመ መንፈስኒ ይፈቱ ዘኢይፈቱ ሥጋ ወሥጋኒ ይፈቱ ዘኢይፈቱ መንፈስ; መንፈስ ሥጋ የማይወደውን፣ ሥጋም መንፈስ የማይወደውን ይወዳል” በማለት ቅዱስ መጽሐፍ ያስተምረናል፡፡

የሁለቱ ነገሮች ተቃርኖ በዚህ ብቻ የሚያበቃም አይደለም፤ ሁለቱም የየራሳቸው የሆነ አበጋዝና የሚያስገኙት ውርስም አላቸው፤ የሥጋዊ ምኞት ምንጭ ዲያብሎስ ሲሆን በባሕርዩ ለእግዚአብሔር የማይገዛ ስለሆነ የእግዚአብሔር ጠላት ነው፤ ለተከታዮቹም ሞትን ያወርሳል፤ የመንፈሳዊ ምኞት ምንጭ ግን የእግዚአብሔር መንፈስ ነውና በባሕርዩ ለእግዚአብሔር ታዛዥ; ተገዥና የዘለዓለም ሕይወትን የሚያወርስ ነው፤ ከዚህ አንጻር ሰው ለሥጋዊ ምኞቱ ተገዢና በሥጋዊ ፈቃድ ተሸናፊ በሆነ ጊዜ ለሥጋውና ለነፍሱ የሚተርፍ ጒዳትን እንደሚያከማች፣ በአንጻሩ ደግሞ ለመንፈሳዊ ምኞቱ ተገዢና ተባባሪ በሆነ ጊዜ ለሥጋውና ለነፍሱ የሚተርፍ ሀብተ ሕይወትን እንደሚያፈራ ዛሬም ግልጽ ሆኖ ይታወቃል፤ ለዚህም የቀዳማዊ አዳም ሥጋዊ ዝንባሌና መንበርከክ፣ የዳግማዊ አዳም (ክርስቶስ) መንፈሳዊ ምከታና ድል ማድረግ ተጨባጭ ማረጋገጫዎቻችን ናቸው፡፡

ቀዳማይ አዳም የዲያብሎስን ምክር ሰምቶ፤ ጣዕመ መብልዕን ሽቶ፣ ለፈቃደ ሥጋው አድልቶ፤ በራሱና በልጆቹ ነፍስና ሥጋ ላይ የሞት ውርስን አውርሶአል፤ ዳግማይ አዳም የተባለ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ በተቃራኒው ጣዕመ መብልዕን ትቶ፣ በኀይለ መንፈስ ተዋግቶ ፣ የዲያብሎስን ፈተና በእግዚአብሔር ቃል መክቶ የአሸናፊነትና የዘለዓለማዊ ሕይወት ርስትን ለእኛ ለልጆቹ አውርሶአል፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ የዚህ ዓለም ወዳጅ የእግዚአብሔር ጠላት ነው ሲል ሜዳው ሸንተረሩ፣ ሣሩ ደንጊያው ወይም ከተማው ገጠሩ ማለቱ እንዳልሆነ ግልጽ ነው፤ በመሆኑም በዚህ ዐውደ ሐሳብ ዓለም ተብሎ የተገለጸው ፍሬ ሐሳብ እግዚአብሔርን የሚቃወም ማንኛውም ፈቃደ ሥጋ ነው፤ ይህ ዐይነቱ ፈቃደ ሥጋ ለእግዚአብሔር የማይገዛ ብቻ ሳይሆን ጠላትም ነው፤ በሰው ላይም ሞትን የሚያመጣ ነውና “እንደ ሥጋ ፈቃድ ብትኖሩ ትሞታላችሁ” ተብሎ ተጻፈ።

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን፤

በነገው ዕለት የምንጀምረው የጾም ሱባዔ ሁለት ዐላማ ያለው ነው፤ ይኸውም አንደኛው ጌታችን በመዋዕለ ጾሙ ፈቃደ ሥጋንና የእርሱ አበጋዝ የሆነው ዲያብሎስን በፈቃደ መንፈስ ድል ማድረጉን ለማሰብ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በሥራው ሁሉ እንድንመስለው ባስተማረን መሠረት እኛም በኀይለ ጾም መሣሪያነት እየታገዝን እንደሱ ፈቃደ ሥጋንና ዲያብሎስን በመዋጋት የፈቃደ ነፍስ ልዕልናን ለማረጋገጥ ነው፤ ይህንም ውጊያ በድል ለማጠናቀቅ የሥጋ መሣሪዎችን ጠንቅቆ ማወቅ አስፈላጊ ነው፤ ሥጋ ነፍስን የሚወጋባቸው የታወቁ መሣሪያዎች አሉት፤ ቅዱስ መጽሐፍ እነሱን እንደሚከተለው በዝርዝር አስቀምጦአቸዋል።

ይኸውም­ ዝሙት፣ ቊጣ፣ ርኵሰት፣ አድመኛነት፣ መዳራት፣ መለያየት፣ ጣዖትን ማምለክ፣ መናፍቅነት፣ ምዋርት፣ ምቀኝነት፣ ጥል፣ መግደል፣ ክርክር፣ ስካር፣ ቅንዐት፣ ዘፋኝነትና ይህንን የሚመስል ሁሉ ይላል፤ በማያያዝም እንደነዚህ ያሉትን የሚያደርጉ ሁሉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም ብሎ ይደመድማል፡፡ ዲያብሎስ እነዚህ የጥፋት መሣሪያዎቹን ተጠቅሞ አዳምንና ሔዋንን ባሳተበት ስልት ሥጋችንን በማስጐምጀትና ጠቃሚ ነገሮች እንደሆኑ አስመስሎ እነሱን በኅሊናችን ውስጥ በማቀጣጠል ወደ መሥገርተ ሞት ወጥመዱ ይከተናል፤ እኛ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች በየጊዜው የምንጾመው እነዚህ የሥጋና የዲያብሎስ የሆኑ መሣሪያዎችን የመንፈስ መሣሪያዎች በሆኑ፡- በፍቅር፣ በቸርነት፣ በመንፈሳዊ ደስታ፣ በእምነት፣ በሰላም፣ በበጎነት፣ በትዕግሥት፣ በየዋህነትና ራስን በመግዛት ለመሰባበርና ከጥቅም ውጭ ለማድረግ ነው፡፡

ከላይ እንደ ተመለከትነው የመንፈስ ቅዱስና የዲያብሎስ መሣሪያዎች ምን ምን እንደሆኑ ተገንዝበናል፤ በአሁኑ ጊዜ በአጠቃላይ በመላው ዓለም በተለይም ደግሞ በሀገራችን ያለውን የሁለቱ አሰላለፍ ምን እንደሚመስል ማስተዋሉ የሚከብድ አይሆንም፤ ሰው ሁሉ መንፈሳዊ ዕውቀቱን ተጠቅሞ፣ የዲያብሎስ መሣሪያ የሆኑትን ጥሎ፣ የመንፈስ ፍሬዎች ወይም መሣሪዎች የሆኑትን አንግቦ፣ ፈቃደ ሥጋንና ዲያብሎስን ቢመክት ኖሮ አሁን እየሆነ ያለው ሁሉ አይከሠትም ነበር፤ ነገር ግን “ሰብእሰ እንዘ ክቡር ውእቱ ኢያእመረ፤ ሰው በተፈጥሮ አዋቂና ክቡር ሆኖ ሳለ በተሰጠው ዕድል መጠቀም አላወቀበትም” ተብሎ በእግዚአብሔር ቃል እንደተገለጸው ያለመታደል ጉዳይ ሆኖ ሊሆን አልቻለም፤ ይሁንና ተወደደም ተጠላ በመጨረሻው ቀን ማለትም በጌታ ቀን ዲያብሎስና መሣሪያዎቹ በኀይለ መንፈስ መሸነፋቸው ብቻ ሳይሆን ከገጸ ምድር ሙሉ በሙሉ መጥፋታቸው አይቀሬ መሆኑ ቅዱስ መጽሐፍ ስለሚነግረን እስከዚያውም ቢሆን በሚጠፋ ነገር ከምንጠፋፋ የማይጠፉትን የመንፈስ መሣሪያዎችን ጨብጠን በሕይወት መኖርን ምርጫችን ብናደርግ ከጥበበኞች ሁሉ የምንበልጥ ጥበበኞች እንሆናለን፡፡

ለመጪው ሕይወት ብቻ ሳይሆን አሁን ላለንበት ጊዜያዊ ሕይወትም ቢሆን፡ ከመለያየት ይልቅ አንድነትን፣ ከጥል ይልቅ ፍቅርን፣ ከቊጣ ይልቅ ትዕግሥትን፣ ከመናፍቅነት ይልቅ እምነትን፣ ከርኵሰት ይልቅ ቅድስናን፣ ከመግደል ይልቅ ማዳንን፣ ከአድመኝት ይልቅ ሰላምን፣ ከስካር ይልቅ ራስ መግዛትን፣ ከዘፋኝነት ይልቅ ዘምሮን እጅግ እንደሚበልጥ ሁላችንም እንስማማበታለን፤ ነገሩ እውነትና ዘላቂ ሐቅ ስለመሆኑ ከስምምነታችን የበለጠ ማስረጃ ሊገኝ አይችልም፤ ስለሆነም በዚህ የጾም ወቅት እነዚህን ለመተግበር ክርስቲያኖች በቀንም፣ በሌሊትም ሊተጉ ይገባል፡፡

በመጨረሻም፡ መዋዕለ ጾም ማለት ፈቃደ ሥጋን ጆሮ ዳባ ልበስ ብለን ለፈቃደ ነፍሳችን ብቻ የምንታዘዝበት፣ የእግዚአብሔርን ድምፅ ብቻ እየሰማን ለእርሱ የምንገዛበት ጊዜ ነው፤ የእግዚአብሔር ድምፅም ፍቅር፣ ሰላምና አንድነት መሆኑን ተገንዝበን ከሁሉ በላይ ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ነዳያን ወንድሞቻችንን በመመገብና በማልበስ ሁሌ ከጎናቸው ሳንለይ ወርኀ ጾሙን እንድናሳልፍ አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ወርኀ ጾሙን አስፈጽሞ ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም ያድርሰን፡

እግዚአብሔር ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ይቀድስ፤ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32019-03-04 13:48:222025-01-28 13:49:39የካቲት 25 ቀን 2011 ዓ.ም. የዐቢይ ጾም መግቢያ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጥር 11 ቀን 2011 ዓ.ም. በጥምቀት በዓል በጃንሜዳ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥር 11 ቀን 2011 ዓ.ም. በጥምቀት በዓል በጃንሜዳ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥር 11 ቀን 2011 ዓ.ም. በጥምቀት በዓል በጃንሜዳ የተሰጠ... Link to: መጋቢት 22 ቀን 2011 ዓ.ም በዓለ ደብረ ዘይት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: መጋቢት 22 ቀን 2011 ዓ.ም በዓለ ደብረ ዘይት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ መጋቢት 22 ቀን 2011 ዓ.ም በዓለ ደብረ ዘይት ቃለ ምዕዳንና...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top