
የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች
የቤተ ክርስቲያናችን ዓላማ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ማስተማርና መንፈሳዊ አገልግሎትን ለእግዚአብሔርና ለሕዝበ ክርስቲያኑ ማበርከት ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ሳይዛባ፣ ሳይፋለስ፣ ፈሩን ሳይለቅ በነበረበት ለማስቀጠል የመንበረ ሐዋርያት ወራሾች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በዓመት ሁለት ጊዜ በቋሚነት እየተሰበሰቡ፣ ስለአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ እየገመገሙ፣ እየመከሩና እየወሰኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን እምነትዋንና ሥርዓቷን እንዲጠብቁ ቅዱሳን አበው በቀኖና ቤተ ክርስቲያን ደንግገዋል፡፡
በፌስቡክ ያግኙን


ከግንቦት 05 ቀን እስከ ግንቦት 06 ቀን 2012 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡
በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቍጥር 164 ድንጋጌ መሠረት ከግንቦት 4 እስከ ግንቦት 6 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ የተካሄደውን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ውሳኔዎች፤

ግንቦት 05 ቀን 2012 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
“ትግሁ ወጸልዩ ከመ ኢትባኡ ውስተ መንሱት፤ ወደፈተና እንዳትገቡ ተግታችሁ ጸልዩ” (ማቴ-6፡1)፡፡

መጋቢት 23 ቀን 2012 ዓ.ም፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የኮሮና ቫይረስ እንዳይስፋፋ ምእመናን በቤታቸው ሆነው እንዲጸልዩ መግለጫ ሰጠ፡፡
መጋቢት 23 ቀን 2012 ዓ.ም

መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ካህናትና ምእመናን ከኮሮና ቫይረስ ራሳቸውን እንዲጠብቁ መመሪያዎች አስተላልፏል፡-
መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም

የካቲት 11 ቀን 2012 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የእነ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን ሥልጣነ ክህነት በውሳኔ ማገዱን ቅዱስነታቸው እንደሚከተለው ገልጸዋል፡፡
የካቲት 11 ቀን 2012 ዓ.ም.