• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ከግንቦት 10 ቀን እስከ ግንቦት 25 ቀን 2014 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ በዓመት ሁለት ጊዜያት እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቊጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልአተ ጉባኤው የመክፈቻው ሥርዐተ ጸሎት ከተፈጸመበት ግንቦት 9 ቀን 2014ዓ.ም. ጀምሮ የተለመደውን ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ሲያካሂድ ሰንብቶ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን የሚበጁ ማኅበራዊና መንፈሳዊ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-

1. የ2014ዓ.ም. የግንቦቱ ርክበ ካህናት ጉባኤ መክፈቻ ንግግር በቤተ ክርስቲያናችንና በሀገራችን የተከሠተውን የሰላም ዕጦት ተከትሎ የደረሰው የሰው ሕይወት ኅልፈትና የአብያተ ክርስቲያናት መቃጠል የካህናትና የምእመናንን ኅልፈተ ሕይወት ላይ ያተኰረ ሲሆን፤ በዚሁ ላይ የተነጋገረው ምልአተ ጉባኤ በሰፊው ተነጋግሮ ችግሩ መፍትሔ እንዲያገኝ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡
2. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተከናወነው የመንፈቅ ሪፖርት፣ ምልአተ ጉባኤ ያዳመጠና የገመገመ ሲሆን በስድስት ወራት ውስጥ ተወስነው ፍጻሜ ያላገኙ ጉዳዮች አስፈላጊው ክትትል እየተደረገ ፍጻሜ እንዲያገኙ ጉባኤው መመሪያ ሰጥቷል፡፡
3. ሀገራዊ ሰላምን አስመልክቶ፣ በችግሩ ዙሪያ የተነጋገረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በአሁኑ ደረጃ በሀገራችን ያለው የሰላም ዕጦት ላይ በሰፊው ተወያይቶ በቀጣይ ጦርነትና የእርስ በርስ ግጭት ተወግዶ አጠቃላይ ሰላም በሚሰፍንበት መልኩ ተነጋግሮ ችግሩን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍታት እንዲቻል፣ ቤተ ክርስቲያናችን የአስታራቂነት ሚናዋን መጫወት እንድትችል ለማድረግ ለፌዴራል መንግሥት ጥያቄ እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡
4. ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገራችን በተከሠተው የሰላም ዕጦት ምክንያት በቤተ ክርስቲያናችንና በካህናት አገልጋዮቻችን እንዲሁም በምእመናኖቻችን ላይ የደረሰውና እየደረሰ ያለው የሰው ሕይወት መጥፋትና የአብያተ ክርስቲያናት መቃጠል፣ የበዓል ማክበሪያ ቦታዎች መነጠቅን አስመልክቶ ጉባኤው የተነጋገረ ሲሆን አጥፊዎች ለሕግ እንዲቀርቡ፣ በቀጣይም በመንግሥት በኩል አስፈላጊው ጥበቃ እንዲደረግልን በመጠየቅ፣ እስከ አሁን በቤተ ክርስቲያናችን ላይ ደረሰ የተባለው ችግር በዐይነትና በቊጥር ተለይቶ ለሚመለከታቸው የፌዴራልና የክልል መንግሥት አካላት እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡
5. በሀገራችን በተከሠተው ወቅታዊ ችግር ምክንያት ችግር ለደረሰባቸው ለተፈናቀሉና ለተሰደዱ ወገኖች፣ ለፈረሱና ለተቃጠሉ አብያተ ክርስቲያናት ማቋቋሚያ፣ ለተዳከሙ የአብነት ት/ቤቶች መደጐሚያ የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ ተወስኗል፡፡
6. በትግራይ ክልል የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቤተ ክርስቲያኒቱን አስመልክተው በ30/04/2014 እና በ3/06/2014 ዓ.ም. ባወጡት መግለጫ ምልአተ ጉባኤው ገምግሞ በቀጣይ የክልሉ አባቶች በማእከል እንደ ቅዱስ ሲኖዶስ አባልነታቸው ለሀገር አንድነትና ሰላም በጋራ እንዲሠሩ ምልአተ ጉባኤው ጥሪውን አቅርቧል፡፡
7. ቤተ ክርስቲያናችን በዘመናት በርካታ የልማት ተግባራትን ስታከናውን የቆየች ቢሆንም ለቤተ ክርስቲያኒቱ አገልግሎት የሚሰጥ የሕክምና ማዕከል ሳታቋቁም መቅረቷ ተገቢ አለመሆኑን በመገምገም፣ በቀጣይ የሕክምና ማዕከሉ ቅድሚያ ተሰጥቶት እንዲገነባ ጉባኤው ወስኗል፡፡
8. በየሦስት ዓመቱ የሚደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ እና የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅን አስመልክቶ በተደረገው ምርጫ፡-

1. ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የሰሜን አሜሪካ ኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ፣

2. ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳር ከተማ ልዩ ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ አድርጎ በመምረጥ ለቀጣይ ሦስት ዓመታት እንዲሠሩ ሰይሟል፡፡

9. በአጠቃላይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በጉባኤ ላይ በቆየባቸው ቀናት ባደረገው ሰፊ ውይይት፡-
• ለቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት መጠናከር፣
• ለሀገራችን፣ ለሕዝባችንና ለመላው ዓለም ሰላም መገኘት፣
• ለተሰደዱና ከቀያቸው የተፈናቀሉ መረጋጋትና ወደ ቀያቸው መመለስ፣
• በሀገራችን ጦርነትና የሰላም ዕጦት በሚወገድበት ሁኔታ በሰፊው በመምከርና ለዘለቄታዊ ሰላም አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ በርካታ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡

በመሆኑም መላው ሕዝባችንና የመንግሥት መሪዎች ሁሉም ለሀገራችን ሰላምና አንድነት ከምንጊዜወም በላይ በአንድነት በመነሣ በትኵረት እንዲሠሩ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

በመጨረሻም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ከግንቦት 9-25 ቀን 2014ዓ.ም. በቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊና ማኅበራዊ እንዲሁም ሀገራዊ ሰላምን አስመልክቶ ሲወያይ በመቆየት በዛሬው ዕለት ስብሰባውን በጸሎት ዘግቷል፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ለሀገራችንና ለቤተ ክርስቲያናችን
እንዲሁም ለመላው ሕዝባችን ሰላሙንና አንድነቱን ይስጥልን፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32022-06-02 10:21:212025-01-27 10:22:11ከግንቦት 10 ቀን እስከ ግንቦት 25 ቀን 2014 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ... Link to: ነሐሴ 1 ቀን 2014 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የፆመ ፍልሰታ መግባትን አስመልክተው የተላለፈ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ነሐሴ 1 ቀን 2014 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የፆመ ፍልሰታ መግባትን አስመልክተው የተላለፈ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ነሐሴ 1 ቀን 2014 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የፆመ ፍልሰታ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top