• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ነሐሴ 1 ቀን 2014 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የፆመ ፍልሰታ መግባትን አስመልክተው የተላለፈ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገር ውስጥም ሆነ በመላው ዓለም ዙሪያ የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት፣
እንዲሁም ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ እንኳን ለጾመ ፍልሰታ ለማርያም በሰላም አደረሳችሁ።

“ወተዘከረ ሣህሎ ዘይቤሎሙ ለአበዊነ ለአብርሃም ወለዘርዑ እስከ ለዓለም፤ ለአባቶቻችን ለአብርሃምና ለዘሩ የነገራቸውን ይቅርታውን ለዘለዓለሙ አሰበ” (ሉቃ.፩፥፶፭)፣ ማኅደረ መንፈስ ቅዱስ የሆነች እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ እግዚአብሔርን ባመሰገነችበት ምስጋናዋ፣ ከላይ የተጠቀሰውን ይህንን አረፍተ ነገር መናገሯን በቅዱስ ወንጌል ተጽፎልናል፡፡
ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምስጋናዋ የገለጸችው ዐቢይ መልእክት የክብር አምላክ እግዚአብሔር የተናገረውን የማያስቀር አምላክ መሆኑን ነው፤ ኤልሻዳይ እግዚአብሔር የተስፋ አምላክ ነውና በየጊዜው ለፍጡራኑ የተስፋ ቃል ይሰጣል፣ ቃል ኪዳንም ይገባል፣ እግዚአብሔር በክዋኔው ዘለዓለማዊ እንደሆነ ሁሉ ቃል ኪዳኑም ዘለዓለማዊ እንደሆነ “ወተዘከረ ኪዳኖ ዘለዓለም፣ ማለትም ዘለዓለማዊ ቃል ኪዳኑን አሰበ” በማለት ቅዱስ መጽሐፍ ያስተምረናል፡፡ እግዚአብሔር መፍቀሬ ሰብእ ከሆነ አምላካዊ ጠባዩ በመነጨ ፍቅሩ ከመጀመሪያው ሰው ከአዳም ጀምሮ ለአበው ቃል ኪዳን እንደገባላቸው ተጽፎልናል፣ ይልቁኑም ለአብርሃም “በዘርእከ ይትባረኩ ኲሎሙ አሕዛበ ምድር ማለትም የምድር አሕዛብ ሁላቸው በዘርህ ይባረካሉ” ብሎ ለዓለም ሁሉ የሚሆን በረከትና ድኅነት ከእርሱ እንደሚገኝ ቃል ኪዳን ገብቶለታል፤ ቅድስት ድንግል ማርያም “ለአብርሃምና ለዘሩ የተናገረውን ቃል አሰበ” ብላ የገለጸችውም ይህንን ቃል ኪዳን ነው፤ ምክንያቱም የምድር አሕዛብ ሁሉ የሚባረኩበት ዘር ኢየሱስ ክርስቶስ በወቅቱ በማሕፀኗ እንዳለ ታውቃለችና ነው፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት፤

ከቅድስት ድንግል ማርያም ምስጋና የምንማረው ዐቢይ ትምህርት ሁሌም የእግዚአብሔርን ድንቅ ፍቅር በማስታወስ፣ በመናገርና በመመስከር ማመስገን፣ ማሰብና ማስታወስ እንደሚገባን ነው፡፡ እግዚአብሔርም ይህንን እንደሚወድ “ወተዘከሩ መንክሮ ዘገብረ፤ ያደረገውን ድንቅ ሥራ አስቡ” ብሎ ነግሮናል፡፡

እግዚአብሔር የተናገረውን የማያስቀር ታማኝ አምላክ ነውና ለአብርሃምና ለዘሩ የገባውን ቃል ኪዳን እነሆ ከዛሬ ሁለት ሺሕ ዐሥራ አምስት ዓመታት በፊት ቃል ኪዳኑን እንደተስፋ ቃሉ በተግባር ፈጽሞአል፤የምድር አሕዛብ ሁሉ የሚባረኩበት ወይም የሚድኑበት ዘር እርሱም መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የአብርሃም ዘር ከሆነች ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ የምድር አሕዛብ የሆነውን በሙሉ በደመ መስቀሉ ባርኮ አንጽቶና ቀድሶ አድኖአል፡፡ እግዚአብሔር የምድር አሕዛብ ሁሉ በምሕረትና በይቅርታ እንድንባረክበት የሰጠን ዘር አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ ሁላችንም መገንዘብና ማመን ይገባናል፣ ይህንን ማወቅ፣ ማስተዋልና ማመን ብፅዕና ማግኘትን ያስከትላል፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያም “ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ነሽ ይሉኛል” ስትል የተናገረችው ቃለ ትንቢት የእግዚአብሔር ማደሪያ ቤተ መቅደስ መሆኗን ስለተረዳች ነው፡፡

እኛም እንደ እሷ “አንትሙ ውእቱ ታቦቱ ለመንፈስ ቅዱስ ማለትም እናንተ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ናችሁ” ተብለናል፤ ቅድስት ድንግል ማርያም ማኅደረ መንፈስ ቅዱስ (መለኮት) የሆነችው በሃይማኖት በትሕትና ነው፤ ከዚህ አንጻር እኛም በሃይማኖት ጥላ ሥር ሆነን በትሕትና በፍቅር በአንድነት የምንኖር ከሆነ የእግዚአብሔር ማደሪያ ለመሆናችን ሌላ ምስክር አያስፈልገንም፡፡ ምክንያቱም ጌታችን “ተፋቀሩ በበይናቲክሙ ወእምከመ ተፋቀርክሙ በበይናቲክሙ የአምረክሙ ዓለም በዝንቱ ከመ አርዳእየ አንትሙ፤ እርስ በርሳችሁ አብዝታችሁ ተፋቀሩ፤ እርስ በርሳችሁ ከተዋደዳችሁ ደቀመዛሙርቴ እንደሆናችሁ ዓለም በዚህ ያውቃል” ብሎ እንዳስተማረን ምስክሮቻችን ፍቅር አንድነትና ትሕትና ይሆናሉና ነው፡፡

የተወደዳችሁ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት፤

ከነገው ዕለት ጀምሮ የምንጾመው የጾመ ማርያም ዋና ዐላማ ጠብንና ጥላቻን ማሸነፍ የሚያስችል የይቅርታን የፍቅርንና የአንድነትን ኀይል በመለኮት ፈቃድ ለማጐልበት ነው፤ የተለየ የጾም፣ የጸሎት፣ የንስሓ ጊዜ ወስኖ እግዚአብሔርን መለመንና ከእርሱ ጋር መገናኘት ከጥንት ጀምሮ የሃይማኖት መርሕ ነው፡፡ በዚህ መርሕ ተመርተው ሕዝባቸውንና ሀገራቸውን ከመከራና ከፈተና የታደጉ ቅዱሳን ብዙ ናቸው፡፡ የልቡናቸውን መልካም ምኞት ያገኙም እንደዚሁ ብዙ ናቸው፡፡

እኛም ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን በደነገገችው የቀኖና ድንጋጌ መሠረት የምንጾመው ጾመ ማርያም፣ ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታችን የልቡናቸውን መሻት እንዲፈጽምላቸው የጾሙትና የለመኑትን ያገኙበት ኩነት መነሻ አድርገን እግዚአብሔር እንደነርሱ የልቡናችንን መሻት እንዲፈጽምልን በማመንና ተስፋ በማድረግ ነው፤ ከዚህ አንጻር የቅድስት ድንግል ማርያም ነገረ ትንሣኤ ወፍልሰት በማሰብ ከእግዚአብሔር ጋር ለመገናኘት በብርቱ እንጥራለን፣ እንጾማለን፣ እንጸልያለን፣ በንስሓም ወደ እርሱ እንቀርባለን፣ ቅዱስ ምሥጢረ ቊርባንንም እንቀበላለን፤ በዚህም ከእግዚአብሔር ጋር እንገናኛለን፡፡ ይህ ሲሆን እግዚአብሔር የልባችንን መሻት በብሩህ ገጽ ተቀብሎ ይፈጽምልናል፡፡ ሁላችንም እንደምንገነዘበው በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት ፍጹም ሰላም ያላት ሀገር እንድትኖረው ነው፤ ይህ ትክክለኛ ፍላጎት ነው፡፡ ይሁንና ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ ሁሉም ነገር ስለማይሆን ፍጹም ሰላም በሀገር ሰፍኖ ሕዝባችን እግዚአብሔር በሰጠው ምድር በፍቅር፣ በአንድነት በነፃነትና በእኩልነት እንዲኖር ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ሁሉ በዚህ ወቅት የቅድስት ድንግል ማርያምን ጸሎትና ስእለት ተማሕፅኖና አስተበቊዖት አጋዥ አድርገን በልዩ ሱባዔ ወደ እግዚአብሔር በመቅረብ በንስሓ፣ በጾም፣ በጸሎት፣ ነዳያንን በመርዳትና ቅዱስ ቊርባንን በመቀበል እሱን መማፀን ይኖርብናል፡፡

በመጨረሻም፤ በሀገራችን የተከሠቱት ያላስፈላጊ ግጭቶችን በድርድር ለመፍታት እየተሞከሩ ያሉ አንዳንድ የሰላምና የውይይት ድምፆች ተስፋ ሰጪ ስለሆኑ ሥር ሰደው፣ በተግባር ተተርጉመው፣ ለተጐዳው ሕዝባችን መጠገኛ ይሆኑ ዘንድ፣ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ሁሉ በዚህ ዙርያ በሱባዔው ወቅት ወደ እግዚአብሔር አቤት በማለትና ሂደቱን በመደገፍ የበኩላቸውን ጥረት እንዲያደርጉ፣ መንግሥትም ሆነ የዓለም አቀፉ ማኅበረ ሰብ በዚህ በጎ ሐሳብ እንዲገፉበትና ሕዝባችንንና ሀገራችንን ከጥፋት እንዲታደጉ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ጾሙን የሰላም የስርየት የፍቅር የአንድነት ጾም ያድርግልን፡፤
ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ፤
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32022-08-07 14:23:492025-01-28 14:24:44ነሐሴ 1 ቀን 2014 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የፆመ ፍልሰታ መግባትን አስመልክተው የተላለፈ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ከግንቦት 10 ቀን እስከ ግንቦት 25 ቀን 2014 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ Link to: ከግንቦት 10 ቀን እስከ ግንቦት 25 ቀን 2014 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ ከግንቦት 10 ቀን እስከ ግንቦት 25 ቀን 2014 ዓ.ም የተካሄደው... Link to: መስከረም 1 ቀን 2015 ዓ.ም ርዕሰ ዐውደ ዓመት የዘመን መለወጫ በዓል መግባትን አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ Link to: መስከረም 1 ቀን 2015 ዓ.ም ርዕሰ ዐውደ ዓመት የዘመን መለወጫ በዓል መግባትን አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ መስከረም 1 ቀን 2015 ዓ.ም ርዕሰ ዐውደ ዓመት የዘመን...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top