• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

መስከረም 1 ቀን የ2007 ዓ.ም የዘመን መለወጫ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ፥ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ፤
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤

የመልካም ስጦታ ሁሉ ባለቤት የሆነው እግዚአብሔር አምላክ እንኳን ከ2006 ዓመተ ምሕረት ዘመነ ማርቆስ ወደ 2007 ዓመተ ምሕረት ዘመነ ሉቃስ በሰላም አደረሳችሁ፡፡

“ወዓመቲከኒ ዘኢየኃልቅ — ዘመንህም አያልቅም።»
(መዝ 101÷27)

ሁሉን ፈጥሮ የሚመግብ እግዚአብሔር አምላክ በባሕርዩ ፍጹም ነውና በእርሱ ዘንድ ኅልፈት መለወጥ፤ ማርጀትና የዘመን ፍጻሜ የለም፡፡

እግዚአብሔር አምላክ እርሱ ራሱ ወደር የሌለው ብርሃን ነው፣የሚገለጽበት ዓለምም በሚያስደንቅ ብርሃን ያሸበረቀና ጨለማ የማይፈራረቀው በመሆኑ ዘመን አይቈጠርለትም፡፡ በዚህ ተለዋዋጭ ዓለም የምናየው የዘመናት ኅልፈትና መተካት፣ ኀላፊው የብርሃን ዑደት ከጨለማ ጋር እየተፈራረቀ የሚፈጥረው ሂደት እንደሆነ ቅዱስ መጽሐፍ ያስቀመጠውና እኛም በዐይናችን የምናየው ነው። (ዘፍ. 1÷14-19)

የምንኖርበት ዓለምና ከእርሱ የወረስነው ሁሉ ኀላፊ እንጂ ቀዋሚ ባለመሆኑ ዘመን ጨምሮ ሁሉም ሲያልፍና ሲተካ እናያለን፡፡ የመንፈሳውያን ፍጥረታት መኖሪያ የሆነው ብርሃናዊው ዓለም ግን ዘመን የማይቈጠርለት፣ ኅልፈትና ውላጤ የሌለበት፣ ጨለማ የማይፈራረቅበት፣ የብርሃናት ዑደት የማይታይበት ነው፣ ነዋሪዎቹም እንደዚሁ የማያልፉና የማያረጁ፣ ዘመንም የማይቈጠርላቸው ቀዋሚና ዘለዓለማዊ ሕይወት ያላቸው ናቸው፡፡ በኀላፊው ዓለም ያሉና በብርሃናት ዑደት ምክንያት የሚቈጠሩ ዘመናት ኀላፍያን ቢሆኑም፣ በእነርሱ መሣርያነት ዘመን ወደማይቈጠርለትና ወደ ማያልፈው ብርሃናዊ ዓለም ሊያደርስ የሚችል ሥራ መሥራት ስለሚቻል፣ ዘመናት በሰው ልጅ መንፈሳዊና ሥጋዊ ሕይወት ውስጥ ያላቸው ፋይዳ ከፍተኛ ነው፡፡ የሥራው ዐይነት የተለያየ ቢሆንም፣ ሁለቱም ዓለማት የሚያመሳስላቸውና አንድ የሚያደርጋቸው ነገር ቢኖር ሥራ ነው፤ በሁለቱም ዓለማት ያሉ ፍጡራን በሥራ ተጠምደው እንዲኖሩ እግዚአብሔር ፈጥሮአቸዋል፡፡

ሥራ የመንፈሳዊም ሆነ የሥጋዊ ሕይወታችን መድኅን ነው፣ ለሥራ የተፈጠርን ስለመሆናችን አካላችንና ባሕርያችን ራሱ ይመሰክራል፣ አፍኣዊ አካላችንም ሆነ ውሳጣዊ ባሕርያችን ሥራን ካልሠራ ሰላምና ጤና አያገኝም፤ እግዚአብሔር አምላክ ለሥራ የሚያገለግሉ ውጫዊ መሣሪያዎችን በብዛት ሰጥቶናል፡፡ ከሰጠን ብዙ ስጦታዎች አንዱና ዋነኛው ዘመን ነው፤ ሥራን መሥራት የምንችለው በዘመን ውስጥ ሆነን ነውና ጊዜን በሥራ መጠቀም ትልቅ ብልህነት ነው፣ ዘመን በሥራ ከምንቀድመው በቀር ሮጦ የማይደክም ፍጡር ስለሆነ ለአፍታ እንኳ የማናስቆመው ነገር ነው፡፡ ስለሆነም ጊዜን ለሥራ የማንጠቀም፣ ይልቁንም በተራ ነገርና በአሉባልታ፣ በነገር ትብትብና በጠማማ አስተሳሰብ ጊዜን የምናባክን ከሆነ፣ በአንገት ላይ ሰይፍን እንደመሳብ ይቈጠራል።

ቀደምት ኢትዮጵያውያን አበው የሥራን ክቡርነት ጠንቅቀው በመረዳታቸው እስከዛሬ ድረስ የዓለም ጠበብቶች ሊደርሱበት ያልቻሉ ጥበባዊ ሥራን ሠርተው እንዳስረከቡን በእጃችን ያለ ውድና ብርቅ ቅርስ ምስክር ነው፡፡ በመካከሉ በተፈጠረው ክፍተት ጥበባዊ ሥራችንና ሥልጣኔአችን ለተወሰነ ጊዜ ቆም ቢልም፣ አሁን በአዲስ መንፈስ እየተጋጋለና እየተቀጣጠለ መታየቱ እጅግ የሚያስደስትና የሚያኮራ ነው፤ ኢትዮጵያ ሀገራችን ለብዙ ዘመናት አጥታው የነበረው ይህንን ዕሴት ነው፤ አሁን የሕዳሴ ዘመን ተበሥሮአል፤ ልማቱና እድገቱ በሁሉም መስክ በአራቱም መዓዝን ተጧጡፎአል፣ ይህ የእግዚአብሔር በረከትና ስጦታ ነው፣ ሕዝባችንም ይህ ዕድል እንዳይቀለበስ አጥብቆ መንከባከብና መጠበቅ አለበት፡፡ ሕዝባችን ከልማት፣ ከአንድነት፣ ከሰላምና ከእኩልነት የተሻለ ሌላ ጠቃሚ ነገር ሊኖረው አይችልም፡፡ ስለሆነም በአዲሱ ዘመን ጅምር የልማትና የሰላም ሥራዎቻችንን ከግብ በማድረስ፣ አዳዲስ የልማት ሥራዎችንም በመጀመር የሀገራችንን የሕዳሴ ጒዞ ማፋጠን አለብን፡፡ የተጀመረው የልማትና የእድገት ሥራ ሁሉ ግቡን ሊመታ የሚችለው ሰላም፣ ፍቅር ስምምነት፣ አንድነት መቻቻል፣ መከባበር፤ ፍትሕና እኩልነት የነገሠበት ማኅበረ ሰብ ሲኖረን ነው፤ ስለሆነም እያንዳንዱ ቅን ዜጋ ይህንን በመገንባትና በማስጠበቅ የበኩሉን ሊወጣ ይገባል፣ እያንዳንዱ ዜጋ ሠርቶ ከመልማት በቀር ሌላ አጀንዳ ሊኖረው አይገባም፡፡

በመጨረሻም፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በጤናው ዘርፍ በተለይም በእናቶች የጤና እንክብካቤ፣ በአካባቢያዊ የሰላም ጥበቃ፣ በፈጣን የኢኮኖሚ እድገት፣ በመልካም አስተዳደርና በፍትሕ አሰጣጥ ወዘተ በመሳሰሉት ዐበይት ተግባራት እየፈጸመችው ያለ ተግባር ኢትዮጵያ ሀገራችን በዓለም መድረክ ያላትን ተሰሚነትና ተቀባይነት በእጅጉ የሚያሳድግና መልካም ገጽታችንን የሚያጎላ መሆኑን የተገነዘብንበት ወቅት በመሆኑ ሕዝቡ በቀጣዩ አዲስ ዓመትም ይህንን አጠናክሮ እንዲቀጥልበት መልእክታችንን እናስተላልፋለን፣ አዲሱን ዓመት የሰላም፣ የልማትና የእድገት ዘመን ያድርግልን፡፡

እግዚአብሔር ይባርካችሁ ይቀድሳችሁ አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32014-09-11 12:37:242025-01-28 12:38:43መስከረም 1 ቀን የ2007 ዓ.ም የዘመን መለወጫ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ነሐሴ 1 ቀን የ2006 ዓ.ም የጾመ ፍልሰታ መግቢያ ቃለ በረከት! Link to: ነሐሴ 1 ቀን የ2006 ዓ.ም የጾመ ፍልሰታ መግቢያ ቃለ በረከት! ነሐሴ 1 ቀን የ2006 ዓ.ም የጾመ ፍልሰታ መግቢያ ቃለ... Link to: መስከረም 16 ቀን የ2007 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: መስከረም 16 ቀን የ2007 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ መስከረም 16 ቀን የ2007 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top