• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ከግንቦት 16 ቀን እስከ ሰኔ 1 ቀን 2008 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ስብሰባ በዓመት ሁለት ጊዜያት እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቊጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልአተ ጉኤው የዘንድሮውን መደበኛ የርክበ ካህናት ስብሰባ የጉባኤው መክፈቻ ሥርዐተ ጸሎት ከተፈጸመበት ከበዓሉ ዋዜማ ከግንቦት 16 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ሰኔ 1 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረስ ለ16 ቀናት ያህል ባደረገው ጉባኤ ጠቀሜታ ባላቸው የአጀንዳ ነጥቦች ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፎአል፡፡ ከእነዚህም መካከል የሚከተሉት በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

1. የ2008 ዓ.ም. የርክበ ካህናት ጉባኤን በተመለከተ ቅዱስ ፓትርያርኩ ያደረጉት የመክፈቻ ንግግር እንዳበቃ ጉባኤው ሥራውን ቀጥሏል፡፡
2. የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ዓመታዊ ሪፖርት በጽሑፍ ቀርቦ ጉባኤው ካዳመጠ በኋላ በሪፖርቱ ላይ ውይይት በማድረግ ለወደፊቱ የሚወሰኑት ሁሉ የአፈጻጸም ችግር እንዳይደርስባቸው ክትትል ይደረግ ዘንድ ተወስኗል፤
3. እስከአሁን እየተሠራበት ያለው ቃለ ዐዋዲ የቤተ ክርስቲያናችን መተዳደሪያ ደንብ ወቅቱን ባገናዘበ መልኩ እንዲሻሻል በተሰጠው መመሪያ መሠረት የተዘጋጀው ረቂቅ ቀርቦ ምልአተ ጉባኤው ከተነጋገረበትና ከታየ በኋላ የረቂቁ ዝግጅት በቋሚ ሲኖዶስ ታይቶ እንዲታተም ተወስኗል፤
4. ስለቅዱስ ፓትርያርክ እንደራሴ አስፈላጊነት ጉዳይ ቅዱስ ሲኖዶስ ከተነጋገረ በኋላ የእንደራሴ አስፈላጊነት በምን ዐይነት ሕግ ላይ ተመሥርቶ መመረጥ አለበት የሚለውን በማጥናት ለጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የሚያቀርብ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ያሉበት ሰባት አባላት እንዲመረጡ ተደርጓል፤
5. ተፈጥሮ ባስከተለው ድርቅ ምክንያት በየመጠለያው ለሚገኙ ወገኖች የዕለት ደራሽ ርዳታ፤ ለተፈናቀሉ ወገኖችም ለመልሶ ማቋቋሚያ አገልግሎት የሚውል የገንዘብና የቊሳቍስ ርዳታ ይደረግ ዘንድ ቤተ ክርስቲያናችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች፤ የድርሻዋንም አስተዋፅኦ አድርጋለች፤
6. በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማት የሚያገለግል ሕንጻ መገንባት ይቻል ዘንድ ቦታ እንዲሰጥ ከገዳሙ ማኅበረ መነኮሳት የቀረበውን ጥያቄ ምልአተ ጉባኤው የተቀበለው ስለሆነ፤ በቤተ ክርስቲያኒቱ ማእከላዊ አስተዳደር በኩል ቦታ ተፈልጎ እንዲሰጥ ተወስኗል፤
7. ቅዱስ ሲኖዶስ በየአህጉረ ስብከቱ ክፍት በሆኑ መንበረ ጵጵስናዎች ብቁ የሆኑ ኤጲስ ቆጶሳትን መርጦ ለመሾም ባለው ዕቅድ መሠረት፤
• ፈተናውንና መሰናክሉን ሁሉ አልፈው ዕውቅና ያገኙትን
• በብሔር ዐቀፍና በዓለም ዐቀፍ ትምህርት የበሰሉትን፤
• የወቅቱንም ችግር ይፈታሉ ተብለው እምነት የተጣለባቸውንና የሚጣልባቸውን፤
• ለተልእኮ የሚፋጠኑትን መነኰሳት በመመርመር፣ በማጥናትና በማጣራት ውጤቱን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረስ የሚያቀርብ አስመራጭ ኮሚቴ እንዲቋቋም ተደርጓል፤
8. የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ምደባ በተመለከተ (ሀ) ብፁዕ አባ ያሬድ ሊቀ ጳጳስ የኢትዮጵያ ሱማሌ ሀገረ ስብከት ሥራን እንደያዙ በአርሲ ሀገረ ስብከት (ለ) ብፁዕ አባ እንጦንስ ሊቀ ጳጳስ በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት (ሐ)ብፁዕ አባ ያዕቆብ ሊቀ ጳጳስ በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት፤ (መ) ብፁዕ አባ እንድርያስ ሊቀ ጳጳስ የሊቃውንት ጉባኤ የበላይ ኀላፊነቱን ሥራ እንደያዙ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የበላይ ኀላፊ በመሆን ተመድበው እንዲሠሩ ምልአተ ጉባኤው ተስማምቷል፡፡

9. በውጭ ላሉት አህጉረ ስብከት ጥናት ተደርጎ በቋሚነት የሚሠሩ አባቶች እስከሚመደቡ ድረስ፤
ሀ/ ሰሜን፣ ሰሜን ምሥራቅና ሰሜን ምዕራብ አውሮፓ አህጉረ ስብከት፤ ለጊዜው በብፁዕ አባ ሙሴ የደቡብ ምዕራብና የደቡብ ምሥራቅ አውሮፓ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተደርቦ እንዲሠራ፤
ለ/ አውስትራልያ ሀገረ ስብከት፤ በብፁዕ አባ ሄኖክ የምዕራብ ወለጋና የአሶሳ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተደርቦ እንዲሠራ፤
ሐ/ ምሥራቅ አፍሪካ ኬንያና ጅቡቲ አህጉረ ስብከት፤ በብፁዕ አባ ዳንኤል የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተደርቦ እንዲሠራ፤
መ/ ምሥራቅ አፍሪካ ሰሜን ሱዳንና ግብጽ አህጉረ ስብከት፤ በብፁዕ አባ ሉቃስ በክልል ትግራይ ዞን ወልቃይት ጸገዴ ሰቲት ሑመራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተደርቦ እንዲሠራ ሆኖ በተጨማሪም የትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት የበላይ ኀላፊ ሆነው እንዲሠሩ፤
ሠ/ ደቡብ ሱዳን ሀገረ ስብከት፤ በብፁዕ አባ እስጢፋኖስ የጅማ፣ የኢሉባቦርና ጋምቤላ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተደርቦ እንዲሠራ ሲል ምልአተ ጉባኤው በአንድ ድምፅ ተስማምቶ ወስኗል፡፡
10. በውጭ አህጉረ ስብከት ካሉት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ያለው የሰላሙ ንግግር ይቀጥል ዘንድ ሰላም ለማንኛውም መሠረት መሆኑ ታምኖበት ይህንኑ ሰላም ለማምጣት አስፈላጊው ጥረት ሁሉ እንዲደረግ፤
11. ስለ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ረዳት ሊቀ ጳጳስ ምደባ ጉዳይ ቅዱስ ሲኖዶስ ከተወያየ በኋላ በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 50 መሠረት ብፁዕ አባ ሕዝቅኤል በያዙት የሀገረ ስብከት ሥራቸው ላይ ደርበው እስከ ጥቅምት 2009 ዓ.ም. ድረስ የፓትርያርክ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲሠሩ ተስማምቷል፤
12. በየሦስት ዓመቱ የሚደረገው የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ ምርጫ ካሉት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት መካከል በማወዳደር፡- (ሀ) ብፁዕ አባ ዲዮስቆሮስ ሊቀ ጳጳስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ (ለ) ብፁዕ አባ ሳዊሮስ ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ ሆነው ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት እንዲሠሩ በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርጠዋል፡፡
13. በሕፃናትና ቤተሰብ ጉዳይ ድርጅት ኀላፊነት በቤተ ክርስቲያናችን እየተረዱ የሚያድጉ ዕጓለ ማውታ ሕፃናት በየአህጉረ ስብከቱ መኖራቸው የሚታወቅ ነው፤ ይኸው የሕፃናትና የቤተሰብ ጉዳይ ድርጅት ዕጓለ ማውታ ሕፃናትን በማሳደግና በማስተማር ረገድ ለሀገራችንና ለቤተ ክርስቲያናችን ታላቅ አለኝታ ስለሆነ እስከ አሁን ከነበረው ይዘት በበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በቅዱስ ሲኖዶስ ተወስኗል፤
14. የቤተ ክርስቲያናችን እምነትና ሥርዐተ አምልኮ እስካሁን ድረስ ተከብሮና ተጠብቆ እንደኖረ ሁሉ አሁንም ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ያለው የመንፈሳዊና የማኅበራዊ አገልግሎት መዋቅር በበለጠ ተጠናክሮ ይቀጥል ዘንድ መመሪያ ተሰጥቶአል፤
15. በቤተ ክርስቲያኒቱ ማእከላዊ አስተዳደር ቀልጣፋና ቅንነት የሰፈነበት አሠራር እንዲኖር፤ በየደረጃው የተዘረጉትም የልማት አውታሮች የበለጠ ውጤት እንዲኖራቸው ለማስቻል፤ ከመንበረ ፓትርያርክ ሥራ አስኪያጅ ጀምሮ ሁሎችም የየአህጉረ ስብከቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ኀላፊነት ያለባቸው ስለሆነ ተከታትለው እየሠሩ እንዲያሠሩ ተወስኗል፤
16. በመከናወን ላይ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ፕሮጀክት አጀማመር ሁሉም ኅብረተሰብ እጁን ሲዘረጋ እንደቆየ ሁሉ፤ አሁንም ለፕሮጀክቱ አፈጻጸም መላው ኅብረተሰብ የበኩሉን ድርሻ ይፈጽም ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፤
17. ከሀገራችን ኢትዮጵያ ውጭ ባሉት አንዳንድ አህጉር እየደረሰ ያለውን የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ችግር በጀሮአችን እንሰማለን፤ በዓይናችንም እናያለን፣ ለማስረጃም ያህል፤ በመሬት መንቀጥቀጥ፣ በጎርፍ ማጥለቅለቅና በሰደድ እሳት ዘግናኝ አደጋ የሚደርስ ኅልፈተ ሕይወት፤ በእርስ በርስ የውስጥ ጦርነት የደረሰውና እየደረሰ ያለው ዕልቂት፤ የእግዚአብሔርን ህልውና በሚፈታተኑ አንዳንድ ግለሰቦች ግንዛቤ ጒድለት እየደረሰ ያለው የጦርነት አደጋ፤ በየብስ በውቅያኖሶችና በሰማይ ላይ በሚበሩ አውሮፕላኖች የሚደርሰው ዘግናኝ ዕልቂትና የመሳሰሉት ከሚጠቁሰት መካከል ናቸው፤

ስለዚህ እግዚአብሔር አምላየካችን ጉዳት ለደረሰባቸው መጽናናትን መረጋጋትን እንዲሰጥልን ቅን ልቡና፣ ትሑት ሰብእና ለሚጎድልባቸው የኅብረተሰብ ክፍሎችም ትዕግሥቱን፣ ርኅራኄውን እንዲያበዛልን እንጸልያለን፡፡ ከሁሉም በላይ ለሀገራችንና ለሕዝቦቿ የሚፈለገውን ሰላምና አንድነት እንዲሁም የልማት ውጤት ማምጣት እንዲቻል ሁሉም ኅብረተሰብ ተግባብቶ፣ ተፋቅሮና ተከባብሮ በአንድነት መንፈስ መነሣሣት እንደሚያስፈልገው ቅዱስ ሲኖዶስ አበክሮ ያሳስባል፡፡

በመጨረሻም በሀገራችን ጎልቶ የሚታየው ድኅነት እንዲወገድ የተራበው፣ የተጠማው፣ የታረዘው፣ መሠረታዊ ፍላጎቱ ተሟልቶለት እንዲኖር፣ በሀገራችን ኢትዮጵያ በዓለሙም ሁሉ ሰላም እንዲሰፍን ቅዱስ ሲኖዶስ በመጸለይ ስብሰባውን በጸሎት አጠናቋል፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ፤ ይቀድስ፤ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤አሜን!

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32016-06-08 08:49:362024-12-07 08:51:58ከግንቦት 16 ቀን እስከ ሰኔ 1 ቀን 2008 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ግንቦት 17 ቀን 2008 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ግንቦት 17 ቀን 2008 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ግንቦት 17 ቀን 2008 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ... Link to: ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓ/ም የጾመ ፍልሰታ መግቢያ ቃለ ቡራኬና ምዕዳን Link to: ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓ/ም የጾመ ፍልሰታ መግቢያ ቃለ ቡራኬና ምዕዳን ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓ/ም የጾመ ፍልሰታ መግቢያ ቃለ ቡራኬና...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top