• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ሚያዝያ 11 ቀን 2012 ዓ.ም የበዓለ የትንሣኤ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤ በሕመም ምክንያት በየጸበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤ በእርሱ ያመኑ ሕሙማንን ያድን ዘንድ የታመመው የሞተውና ሞትን ድል አድርጎ የተነሣው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!

“ሐመ ወሞተ ወተቀብረ ወተንሥአ እሙታን አመ ሣልስት ዕለት
ታመመ፣ ሞተ፣ተቀበረ፣ በሦተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። ”
(1ኛቆሮ 15፥3-4)

የክርስቲያኖች መሠረተ ሃይማኖት ወልደ እግዚአብሔር የሆነው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለእኛና ስለ ድኅነታችን ሲል በለበሰው ሥጋ ታመመ፣ ሞተ፣ተቀበረ፣ በሦስተኛውም ቀን ሞትን ድል አድርጎ፣ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ተነሣ የሚለው ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ሁሉ ጸዋትወ መከራ የተቀበለው ያለ ምክንያት አልነበረም፤ እኛ ሰዎች በተከተልነው የተሳሳተ ምርጫ በነፍሳችንም ሆነ በሥጋችን ለጸና ሕመም ተጋልጠን ስለነበረ ለሕመም የተጋለጠውን ሰብኣዊ ባሕርያችን በተዋሕዶ የራሱ ገንዘብ አድርጎ በሕማሙ የሕመማችን ቤዛ በመሆን ሊያድነን ነው፡፡ ይህንን እውን ለማድረግ ከኀጢአት በቀር ሁለንተና ሰብኣዊ ባሕርያችንን በድንግል ማርያም ማሕፀን ተዋሕዶ ሰው ሆኖአል፤ በሠላሣ ዓመቱ ከተጠመቀ በኋላም ለሦስት ዓመታት ያህል ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን አስተምሮአል፤ ሕሙማንን ፈውሶአል፤ ሙታንንም አንሥቶአል፤ ይህ አምላካዊ ኀይል በነፍስም በሥጋም ሊያድነን የመጣ እውነተኛ መድኀኒት እሱ መሆኑን የሚያስገነዝብ ነበረ፡፡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ የታመሙትን በማዳን፣ በኀጢአት የሞቱትን ኀጢአታቸውን ይቅር በማለት፣ በሞትና በመቃብር የተያዙትን ከሞት በማንሣት፣ ፍጹም አዳኝነቱን ለዓለም ካሳወቀ በኋላ፣ የቤዛነታችን መሥዋዕት ለመሆን በፈቃዱ በፍጡራን እጅ ብዙ መከራን በመቀበል ታመመ፤

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን፤

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕሙማንን ያድን ዘንድ መታመሙ አንድ የሚያስገነዝበን ታላቅ ነገር አለ፤ እሱም የሰዎችን መታመም የማይወድና የማይፈቅድ መሆኑ ነው፤ ጌታችን የሰዎች መታመም የማይገደው አምላክ ቢሆን ኖሮ ለሕሙማን ብሎ እስከ መሰቀል ድረስ ደርሶ መከራ ባልተቀበለ ነበር፡፡ ነገር ግን “ሐመ ከመ ሕሙማነ ያድኅን እለ ተወከሉ በላዕሌሁ፤ በእሱ የታመኑትን ያድን ዘንድ ታመመ” እያሉ መጻሕፍት እንደሚነግሩን ለሕሙማን የተሟላ ድኅነትን ያድል ዘንድ እስከ ሞት ድረስ ሕይወቱን አሳልፎ ሰጥቶአል፡፡ በመሆኑም በሕማሙ ሕመማችንን፣ በሞቱ ሞታችንን፣ በመቃብሩ ሙስና መቃብርን አስወግዶ በትንሣኤው ትንሣኤያችንን አብሥሮናል፤ በዚህ የጌታችን ቤዛነት ዕዳችን ሁሉ ከላያችን ላይ ስለተነሣልን በትንሣኤው ላመን ሁሉ የድኅነት ሽልማታችን እሱም ፍጹም መዳናችን ለጌታ ቀን ተዘጋጅቶልን በፊታችን ይጠብቀናል፤ በዚያን ጊዜ በእርሱ ሕመም ሕመማችን ጠፍቶ፣ በእርሱ ሞት ሞታችን ተሸንፎ፣ በእርሱ መቃብር መቃብራችን ባዶ ሆኖ በክብር እንነሣለን፤ በዚያን ጊዜ እኛም እንደ እሱ የማይታመም፣ የማይሞትና መቃብር የማይነካው አካል ተጐናጽፈን ከእርሱ ጋር ፍጻሜ በሌለው ሕይወት በመንግሥቱ እንኖራለን፡፡

በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ተጠብቆልን ያለውን ፍጹምና ሁለንተናዊ ድኅነት በጌታ ቀን እስክንረከብ ድረስ በዚህ ዓለም ባለው ምድራዊ ሕይወታችን ሥጋዊ ሕመም፣ሞተ ሥጋና ለጊዜውም ቢሆን ርደተ መቃብር አይቀርልንም ፡፡ ይህም በመሆኑ በየጊዜው በልዩ ልዩ በሽታ እንታመማለን፣ እንሠቃያለን፣ በመከራም እናልፋለን፣ ነገር ግን ይህ ሁሉ በእኛ ላይ እንዲሆን የእግዚአብሔር ፈቃድና ፍላጎት ነው ወይ? ካልን የመጽሐፍ ቅዱስ መልስ አይደለም የሚል ነው፤ ሕሙማንን ለማዳን የታመመው አምላክ ሕሙማን በልዩ ልዩ በሽታዎች እንዲጠቁ ይፈቅዳል ማለት የማይቻል ነው፤ ይሁን እንጂ ከእግዚአብሔር ቁጥጥር ውጭ የሆነ በሽታ የለምና በሃይማኖታችን፣ በጸሎታችን እሱ በሰጠን አእምሮ ተጠቅመን እንድንከላከል ብቻ ሳይሆን በምንችለው ሁሉ እንድንመክተው እግዚአብሔር ይፈልጋል፡፡ ሁላችንም ከጌታችን አስተምህሮ እንደምንረዳው በእግዚአብሔር የተሰጡ ሕጎች በሙሉ ዐላማቸው ሰውን ለማዳን ብቻ ነው፤ ስቅለቱም፣ ሞቱም፣ ትንሣኤውም የተደረገው ለሰው ነው፤ ሰንበትም የተፈጠረችው ለሰው እንጂ ሰው ለሰንበት አልተፈጠረም፤ እንደዚሁም ሁሉ ጾሙ፣ ጸሎቱ፣ ሱባዔው የተፈጠረው ለሰው ነው፤ ሰው ከሌለ ጸሎቱም፣ ጾሙም፣ ሱባዔውም፣ ሃይማኖቱም ሳይቀር ሌላው ሁሉ የለም፤ ምክንያቱም ይህ ሁሉ የተፈጠረው ለሰው ነውና ሰው ከሌለ ለማን ተብሎ ይደረጋል፤ እግዚአብሔር መጀመሪያውኑ ሲፈጥረን በዚህ ዓለም እንደ ፈቃዱ ልንኖር እንጂ በአሠቃቂ በሽታ ተሠቃይተን ተዋርደንና የሚቀብረን አጥተን እንደቅጠል ረግፈን ልንቀር አይደለም፤ እውነት ነው እግዚአብሔር ይህንን አሠቃቂ የኮረና በሽታ በከሃሊነቱ አንድ ቀን ያስወግደዋል፤ ግን እኛስ በሰጠን አእምሮና ባለሙያዎቻችን በሚነግሩን (በሚሰጡን) ምክር ተጠቅመን የዓቅማችንን ያክል መከላከል የለብንም ወይ? ነው ጥያቄው፤ አዎ መከላከል አለብን እንዲያውም እግዚአብሔር ዕውቀቱን በፈቀደላቸው የጥበብ ባለሙያዎች ልጆቻችን ችግሩንና መፍትሔውን እየነገረን እያለ እግዚአብሔር ያውቃል እያልን ቸል የምንል ከሆነ ጌታችን እንደነገረን እግዚአብሔርን መፈታተን ነው የሚሆነው፤ ይህም ኀጢአትም ነው ፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ምድራዊ ወኪል በሆነው በቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት ምእመናን በቤታቸው ሆነው በመጸለይ የኮረና ቫይረሱን እንዲከላከሉ ያስተላለፈው ውሳኔ እንዲሁ ዝም ብሎ አይደለም፤ ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ራስን የመጠበቅና የመከላከል ውሳኔ ያስተላለፈው፦
(1) እግዚአብሔር አንድ ሰው ስንኳ በጥንቃቄ ጉድለት እንዲጐዳ የማይፈቅድ መሆኑን ስለሚያውቅ፤
(2) አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በቤት ሆኖ መጸለይና መጾም ሱባዔንም መፈጸም የተፈቀደ ብቻ ሳይሆን እንዲያውም እንደዚህ ያለ ችግር ሲያጋጥም “ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በሥውር ላለው አባትህ ጸልይ” የሚል የጌታችን ትእዛዝና ትምህርት መኖሩን ስለሚያውቅ፤
(3) ምእመናንም ሆኑ ካህናት እስካሉ ድረስ እግዚአብሔር ምሕረቱን በላከልን ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አንድ ላይ ሆነን መጸለይ፣ ማመስገንና ማስቀደስ፣ ማምለክና መቊረብ እንደሚቻል በመገንዘብ ነው፤
(4) ምእመናን ከሌሉ ሁሉንም እናጣለን ከሚል አባታዊ ርኅራኄና አርቆ አስተዋይነት በመነሣት እንደዚሁም በተሰጠን ሥልጣን ይህንን ነገር ለሕዝባችን ባናስታውቅ በእግዚአብሔርም በሥነ ምግባርም ከባድ ወቀሣና ተጠያቂነት እንደሚያስከትልብን በመረዳት ነው፡፡

ስለዚህ አሁንም ቢሆን ከቅዱስ ሲኖዶስ በተላለፈውና ለወደፊትም እንደ አስፈላጊነቱ በሚተላለፈው ሲኖዶሳዊ ብይን መሠረት በየቤታችሁ ሆናችሁ ከልብ ወደ እግዚአብሔር በመጸለይ በሽታውን እንድትከላከሉ፣ ለተቸገሩ ወገኖችም ባላችሁ ዐቅም ሁሉ እንድትረዱና እንድታግዙ በእግዚአብሔር ስም አደራችንን እናስተላልፋለን፡፡

በመጨረሻም፤ በእርሱ የታመኑትን ሕሙማን ሊያድን፤ የታመመው፣ የሞተው፣ የተቀበረውና በሦተኛው ቀን ሞትን ድል ነሥቶ የትንሣኤውን የምሥራች ያሰማን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የበሽታውን መጥፋትና መወገድ የምሥራች አሰምቶን የተለመደውን ሃይማኖታዊና ዕለታዊ ተግባራችንን በሰላም እንድናከናውን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን፡፡ መልካም የትንሣኤ በዓል ያድርግልን፣

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ይቀድስ፣ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32020-04-19 14:03:022025-01-28 14:03:57ሚያዝያ 11 ቀን 2012 ዓ.ም የበዓለ የትንሣኤ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: መጋቢት 23 ቀን 2012 ዓ.ም፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የኮሮና ቫይረስ እንዳይስፋፋ ምእመናን በቤታቸው ሆነው እንዲጸልዩ መግለጫ ሰጠ፡፡ Link to: መጋቢት 23 ቀን 2012 ዓ.ም፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የኮሮና ቫይረስ እንዳይስፋፋ ምእመናን በቤታቸው ሆነው እንዲጸልዩ መግለጫ ሰጠ፡፡ መጋቢት 23 ቀን 2012 ዓ.ም፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ... Link to: ግንቦት 05 ቀን 2012 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ግንቦት 05 ቀን 2012 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ግንቦት 05 ቀን 2012 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top