• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

መስከረም 16 ቀን 2011 ዓ.ም. የመስቀል ደመራ በዓል ሐዋርያዊ መልእክት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

የጥል ግድግዳን በመስቀሉ አፍርሶ ሁላችንንም በፍቅርና በይቅርታ አንድ አድርጎ ወደ እርሱ ያቀረበን አምላካችን እግዚአብሔር እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ አንድ ዓመተ ምሕረት በዓለ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ።

«ወወሀበነ ሰላመ ለርሑቃን ወሰላመ ለቅሩባን በመስቀሉ
በመስቀሉ ርቀው ለነበሩትም፥ ቀርበን ለነበርነውም ሰላምን ሰጠን።»
(ኤፌ. 2፥17)

የእግዚአብሔር ቃል እዚህ ላይ እንደሚነግረን ስሕተት ባመጣው ኀጢአት ምክንያት ሰዎች በአንድ ወቅት በመንፈስ ተለያይተውና ተራርቀው እንደ ነበሩ ነው። በእርግጥም የቀደመው ሰው በመስሐቲ ፍጡር ተገፋፍቶ ስሕተትን በመፈጸሙ ለኀጢአት ተዳርጎ ከእግዚአብሔር ተለይቶ፥ ከገነትም ወጥቶ ወደ ምድረ ፍዳ እንደተሰደደ እናውቃለን። በምድረ ፍዳ መኖርን አንድ ብሎ የጀመረው የሰው ልጅ ንጽሐ ባሕርዩ ስለአደፈበት በስሕተት ላይ ስሕተት እየፈጸመ በመቀጠሉ የእርስ በርስ መለያየትና መራራቅ እያሰፋ የጨለማ ሕይወትን ማስተናገድ ቀጠለ። ሰዎች በመለያየትና በመራራቅ የኖሩበት ያ ዘመን የጨለማና የሞት ጥላ ዘመን እንደነበረ ቅዱስ መጽሐፍ ‘በጨለማና በሞት ጥላ የሚኖር ሕዝብ’ እያለ ይገልጸዋል። በዚያን ወቅት ሰዎች ከሰማያውያን ፍጡራን ብቻ ሳይሆን እርስ በርሳቸውም ተለያይተውና ተራርቀው የኖሩበት፥ ከሁሉም በላይ ደግሞ ሕይወት፥ መድኀኒት ከሆነው ከእውነተኛው አምላክ ከእግዚአብሔር ተለይተውና ርቀው፥ በባዕድ አምልኮ ተዘፍቀው የኖሩበት ያ የፍዳ፥ የመርገም፥ የኵነኔ፥ የመለያየትና የመራራቅ ዘመን እውነትም የጨለማና የሞት ጥላ ተምሳሌት ነበረ። ሆኖም የሰው ድኅነቱን እንጂ ጥፋቱን የማይሻ እግዚአብሔር አምላካችን በፍጹም ፍቅሩ እኛን ሊታረቀንና ወደራሱ ሊያቀርበን ቍርጥ ፈቃዱ እንደሆነ በቅዱሳን ነቢያት ደጋግሞ ገለጸልን። ጊዜው ሲደርስም ራሱ በሥጋ ተገልጾ በመስቀል ላይ በፈጸመው ቤዛነት ፍጹም ይቅርታን ሰጥቶ፥ በሩቅም በቅርብም ያለነውን አንድ ላይ አገናኝቶ የአንዲት መንግሥቱ ዜጎች አድርጎናል።

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን፤

የመስቀልን በዓል በየዓመቱ በታላቅ ድምቀት የምናከብርበት ዋና ምክንያት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የራቁትንና የቀረቡትን አሰባስቦ አንድ ያደረገበትን ምሥጢር ተረስቶና ተዳፍኖ እንዳይቀር ሲባል የተካሄደውን መንፈሳዊ ተጋድሎ ለማስታወስና በትምህርተ መስቀል ውስጥ ያለውን የሰላም ጸጋ በምእመናን ልቡና ውስጥ ለማሠረጽ ነው። ከመስቀሉ የምንሰማው እጅግ በጣም ላዕላዊ አስተምህሮ «እየተበደሉም ቢሆን ለበዳዮች ይቅርታ መስጠት፥ በፍቅርም መቀበል» ነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደል ሳይኖረው በዐመፅና በአድማ ተነሣሥተው በችንካር እጁንና እግሩን ቸንክረው፥ በገመድ አስረው ለሰቀሉት ሰዎች በዚያችው ሰዓት በመስቀል ላይ እያለ «የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው» ብሎ ይቅርታ መስጠቱ፥ በመስቀሉ ላይ የተገነባው የይቅርታ፥ የምሕረትና የፍቅር ከፍታ ምን ያህል አስገራሚ እንደሆነ በአድናቆትና በተመስጦ እንድናየው ያስገድደናል። በመሆኑም ከዚህ ዐቢይ በዓል ልንወስደው የሚገባን ዐቢይ አስተምህሮ ፍቅርን፥ ይቅርታንና አንድነትን እንደ ልዩ የሕይወት ጸጋ አድርጎ መያዝ ለዘላቂ ሰላም ዋስትና አለው የሚለው ነው።

ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ጥፋትና በደል በምልአት የሚያውቅ አምላክ ሆኖ ሳለ በመዋዕለ ሥጋዌው ሁሉን በፍቅር እየተቀበለ ይቅር ተብለሃል፥ ይቅር ተብለሻል ከማለት በስተቀር በአንድ ሰው እንኳ አልፈረደም። ታዲያ የተደረገውንና የተነገረውን ብቻ ሳይሆን በልብ የታሰበውንም ሳይቀር የሚያውቅ አምላክ ሁሉንም በፍቅር፥ በይቅርታና በምሕረት የሚቀበል ከሆነ የራሳችንን እንጂ የሌላውን በደል በአግባቡ የማናውቅ፥ በዚያውም ላይ ሌላውን ከምንተችበት በደል ነፃ ሳንሆን ለመፍረድ እንዴት እንደፍራለን? ምክንያቱም መፍረድ በራሱ ኀጢአት እንደሆነ «በማንም ላይ አትፍረዱ» ተብሎ ተነግሮናልና ነው። የመስቀል አስተምህሮ አንድነትና አንድነት ብቻ እንደሆነ የምንገነዘበው ለበደለኞች በተደረገው ይቅርታ ነው። በደለኞች ይቅርታ ከተደረገላቸው ይቅርታ የተደረገላቸው በደለኞችና ያልበደሉ ወገኖች አንድ ላይ ይውላሉ ማለት ነው፤ ታዲያ አንድነት ማለት ይህ አይደለምን? ቅድስት ዕሌኒ ከብዙ ሠራዊቷ ጋር ረጅም ጒዞ የተጓዘችው የፍቅር፥ የይቅርታና የአንድነት አስተምህሮ ዋና መገለጫ የሆነው ዕፀ መስቀል ተቀብሮ፥ ተዳፍኖና ተረስቶ መቅረት የለበትም፥ ዓለምና ትውልዶች ሊማሩበት፥ ሊያውቁትና ሊመሩበት ይገባል በሚል ጽኑ መለኮታዊ እምነት እንደነበረ ጥርጥር የለውም። በመሆኑም ህልምዋና ጥረትዋ ተሳክቶ እነሆ በዛሬው ዕለት በደመረችው ጢሰ ዕጣን አመልካችነት መስቀሉ የተቀበረበትን ለማወቅ ችላለች። ባደረገችውም ቊፋሮ መጋቢት 10 ቀን እውነተኛውን መስቀል ለማውጣት ችላለች። ወዲያውኑም ቤተ ክርስቲያኑን ማሠራት ጀምራ መስከረም 17 ቀን ቅዳሴ ቤቱን በማክበር መስከረም 21 ቀን ዕፀ መስቀሉን በጎልጎታ ባሠራችው ቤተ ክርስቲያን አስገብታለች። እኛም በዓለ መስቀሉን በየዓመቱ የምናከብረው ከዚህ ሃይማኖታዊ ትውፊት በመነሣት ነው።

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን፤

የደመራን በዓል ስናከብር ደመራ ማለት የተበታተኑትንና ተራርቀው የነበሩትን ዕንጨቶች አንድ ላይ ማሰባሰብ ማለት እንደሆነ አንዘነጋውም። ታዲያ ዕንጨቶችን ሰብስቦ አንድ ላይ በመደመር አንድነትንና እውነተኛነትን ያስተማረ ቅዱስ መስቀል አይደለምን? እኛስ ከመስቀል ባገኘነው መሠረታዊ አስተምህሮ ደመራን በመደመር መስቀሉን ለማክበር የተሰበሰብነው አንድነታችንን ለማረጋገጥ አይደለምን? ይህንን ተገንዝበን በዓለ መስቀሉን እያከበርን ከሆነ የመስቀሉ ትምህርት በሚገባ ገብቶናል ማለት ነው። መስቀል ማለት ወዳጅን ብቻ ሳይሆን ጠላትንም ጭምር እንደራስ አድርጎ መውደድ ነው፤ መስቀል ማለት ለወዳጅ ብቻ ሳይሆን ለበዳይም ጭምር ይቅርታን መጸለይ ነው፤ መስቀል ማለት ከወዳጅ ጋር ብቻ ሳይሆን ከባላጋራም ጋር ታርቆና ተቻችሎ በአንድነት መኖር ነው። ይህ ዐይነቱ ሕይወት ሰዎችን ወደ ፍጹም ፍቅር ያደርሳቸዋል። ፍቅርና ይቅርታ ሲጠቅሙ እንጂ ሲጎዱ ታይተው አያውቁም። ለዚህም ነው ሕዝባችን በየዓመቱ በመላ ሀገራችን በሚከበረው በዓለ መስቀል የተጣላው ታርቆና ይቅር ይቅር ተባብሎ በየሰፈሩ በአንድነት ተቀምጦ እግዚአብሔር የሰጠውን በረከተ ማእድ በኅብረት እየተቋደሰ አንድነቱንና ፍቅሩን የሚያድሰው። ቅዱስ መስቀል ያወረሰንን ይህንን ባህል እናክብረው፥ እንጠብቀው፥ እንመራበት።

በመጨረሻም፤ በዛሬው ዕለት ለመላ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት የምናስተላልፈው የእግዚአብሔር መልእክት ገና ያልሰከኑ የሚመስሉ የጥላቻ፥ የመጠራጠር፥ የመለያየትና ያለመተማመን፥ ራስን የመውደድና የመሳሰሉ ዝንባሌዎች እንዲገቱ፥ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ አንድነት ከሁሉም በላይ እንደሆነ እንዲገነዘቡ፤ ኀይልና ጒልበት፥ እድገትና ብልጽግና፥ መከበርና መታፈር፥ መወደድና መፈራት በአስተማማኝ ሁኔታ የሚገኘው ከአንድነት ብቻ እንደሆነ በአጽንዖት እንዲያስተውሉ፤ ከእኛ ውስጥ አንድ ስንኳ ሳይጠፋ በሰላም ዘመኑን የይቅርታና የአንድነት ዘመን አድርገው እንዲቀበሉና ይህንንም እንዲጠብቁ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

በዓለ መስቀሉን የሰላም የፍቅርና የአንድነት በዓል ያድርግልን እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር። አሜን።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32018-09-26 13:42:542025-01-28 13:43:55መስከረም 16 ቀን 2011 ዓ.ም. የመስቀል ደመራ በዓል ሐዋርያዊ መልእክት
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የመስከረም 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ዘመን መለወጫ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: የመስከረም 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ዘመን መለወጫ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የመስከረም 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ዘመን መለወጫ በዓል ቃለ... Link to: 37ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ጥቅምት 5 ቀን 2011 ዓ.ም አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ Link to: 37ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ጥቅምት 5 ቀን 2011 ዓ.ም አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ 37ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ጥቅምት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top