• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ነሐሴ 1 ቀን 2010 ዓ.ም. የጾመ ፍልሰታ ሙሉ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ወምእመናት በሙሉ እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥር ዓመተ ምሕረት የቅድስት ድንግል ማርያም ተዝካረ ጾም በሰላም አደረሳችሁ፡፡

“ወአፅገቦሙ እምበረከቱ ለርኁባን
የተራቡትን ከበረከቱ አጠገባቸው፤”
(ሉቃ. 1፥53)

ይህ ቃል፤ መንፈሰ እግዚአብሔር በቅድስት ድንግል ማርያም ልሳን በኩል ያስተላለፈው መለኮታዊ ቃል ነው፡፡ የቃሉ መሠረታዊ መልእክት በድንግል ማርያም ማሕፀን ካደረው ከጌታችን ከመድኀኒታችንና ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ነገረ አድኅኖ ጋር በቀጥታ የተያያዘ ነው፤ ረኃብ የሚለው ቃል ሰፋ ተደርጎ ሲታይ በረኃበ ሥጋ ላይ ብቻ ሳይሆን በሰው ልጅም ሆነ በሌሎች ሕያዋን ፍጡራን የሚከሠት የመሠረታዊ ፍላጎት ዕጥረትን የሚገልጽ ነው፡፡ ይህም የዕውቀት፣ የጤና፣ የመንፈሳዊ ሕይወት፣ የሞራል፣ የሰላም አለመረጋጋትን የሚያከስትሉ የህልውና ጣዕም ዕጥረቶችን በሙሉ ሊያመለክት ይችላል ማለት ነው፡፡

በተለይም በአምሳለ እግዚአብሔርና፣ በአርኣያ እግዚአብሔር የተፈጠረውና ሕያው መንፈስ ያለው የሰው ልጅ ከመንፈሳዊ ሕይወት ርቆ ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኝነት ሲያቋርጥ ከባድ የሆነ መንፈሳዊና ሞራላዊ ረኃብ ያጠቃዋል፡፡ ይህ ዐይነቱ ረኃብ ከሁሉም የባሰ ጎጂ ረኃብ ነው፤ ሰው በአምላኩ እስካመነ ድረስ በጸሎትና በሃይማኖት ፈጣሪውን ተማፅኖ በፈጣሪ በረከት ተግባሩ ሰምሮለት ረኃበ ሥጋንና ሌሎች መሰል ዕጥረቶችን ሊያስወግድ ይችላል፡፡ ከእግዚአብሔር በመለየቱ የሚያጋጥመው ረኃበ ነፍስ ግን በዚህ ዓለም ባለበት ጊዜ ጎልቶ ባይታይም በወዲያኛው ዓለም የከፋ ረኃበ ነፍስ ያገኘዋል፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እናንተ አሁን የምትራቡ ብፁዓን ናችሁ ትጠግባላችሁና፤ እናንተ አሁን የጠገባችሁ ወዮላችሁ ትራባላችሁና” ሲል ያስተማረው ረኃበ ሥጋውን ከፅጋበ ነፍስ፣ ፅጋበ ሥጋን፣ ከረኃበ ነፍስ አዟዙሮ በማነፃጸር እንደሆነ መረዳት ይቻላል፡፡ ከዚህ አኳያ ሲታይ ከረኃበ ሥጋ ይልቅ ረኃበ ነፍስ እጅግ በጣም ከባድ እንደሆነ እናስተውላለን፤ በሌላ በኩል ረኃብ ማለት የእግዚአብሔርን ቃል ያለመስማት እንደሆነ ሲያመለክት እግዚአብሔር በነቢዩ አድሮ “ረኃብሰ ኢሰሚዐ ቃለ እግዚአብሔር፣ ረኃብ ማለት የእግዚአብሔርን ቃል ያለመስማት ነው ብሎአል” ከዚህ አንጻር መንፈስ ቅዱስ ባደረባት እግዚአብሔር ወልድ ማሕፀኗን መንበረ መንግሥት ባደረገላት በቅድስት ድንግል ማርያም ልሳን የተጠቀሰው ረኃብና ጽጋብ የትኛው ነው ብለን ብንጠይቅ መልሱ ከባድ አይሆንም፤ እግዚአብሔር የፍጥረቱን ረኃበ ሥጋ የማይሻ ሩኅሩኅ አባትና ፈጣሪ ቢሆንም ከሥጋዊ ይልቅ ለመንፈሳዊ፣ ከጊዜያዊ ይልቅ ለዘለዓለማዊ ሕይወት እንደሚያደላ የታወቀ ነው፤ ለሰው ልጅ ሁሉ ቤዛ ይሆን ዘንድ ወደዚህ ዓለም የመጣበት መሠረታዊ ዐላማም ይኸው ነው፤ ከዚህ አኳያ ከላይ የተጠቀሰው በረከት ከበረከተ ሥጋ በላይ የሆነ በረከተ ነፍስን የሚያመለክት ነው፡፡

ክርስቶስ ሰው ከመሆኑ በፊት በዓለም ሁሉ ተንሰራፍቶ የነበረውና መድኀኒት ያልተገኘለት የምግብ ረኃብ ሳይሆን የመንፈሰ ልደትና የመንፈሰ ሕይወት ዕጦት ነው፤ ይህ ዕጦት ነው ረኃብ ተብሎ የተገለጸው፣ ቅዱስ ገብርኤል ሊያበሥር የመጣውም መንፈሳዊ በረከትን፣ እርሱም ከእግዚአብሔር ጋር በሐዲስ ልደት መገናኘትን፣ ለሰው ልጅ ሁሉ የሚናኝበት ዕድል ከእግዚአብሔር የተዘጋጀ መሆኑን በቅድስት ድንግል ማርያም በረከት በኩል ሊያበሥር ነው፤ የበረከቱ መጀመሪያ ቅድስት ድንግል ማርያም መሆኗን ለማሳየትም እግዘአብሔር ካንቺ ጋር ነው በማለት ገልጾታል፡፡ እንግዲህ ትልቁ ረኃብ እግዚአብሔርን ማጣት፣ ትልቁ በረከት ደግሞ እግዚአብሔርን ማግኘት እንደሆነ ከዚህ መረዳት ይቻላል፤ ከቅድስት ድንግል ማርያም በፊት የነበረው ዘመን ዓመተ ፍዳ ፣ ዓመተ ኵነኔ በመሆኑ በእነዚያ ዘመናት የነበረው ትውልድ ሁሉ ከረኃበ ሥጋ ይልቅ መንፈሳዊ ረኃብ ያጠቃው ነበረ፤ በምድራዊ ሕይወቱም በአምልኮ ጣዖት፣ በክሕደት፣ በብልሹ ሥነ ምግባር፣ በቀቢጸ ተስፋ፣ በጽልመተ አእምሮ የተዋጠ፣ በሰማያዊ ሕይወቱም በኵነኔ ነፍስ በግዞት ከሰይጣን ሠራዊት ጋር በሥቃይ የሚማቅቅ ነበረ፤ ይህ ሁሉ በግዙፉ ዓለም ከሚታወቀው ረኃበ ሥጋ የባሰ ነበረ፤ ቅድስት ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ የተናገረችው ረኃብ እሱ ነው፤ በረከቱም በማሕፀኗ የተሸከመችው ምሉአ ጸጋ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ከበረከቱ አጠገባቸው የተባሉትም በእሱ አምነው የተጠመቁ፣ በደሙ ነጽተው ከሱ ጋር የተዋሐዱ ናቸው፤ ይህንን ያደረጉ ምእመናን ከእግዚአብሔር ጋር በትክክል ተገናኝተዋል፤ በረከቱም በምልአት አድሮባቸዋል፡፡ ምድራዊ ረኃብ እንኳ ቢያጋጥማቸው በሰማያዊ ተስፋ ተሞልተው ሁሌም እንደጠገቡ፤ በሰማያዊውም ዓለም ከእርሱ ጋር ነግሠው ከብረው በደስታ ይኖራሉ።

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን፤

የቅድስት ድግል ማርያም በዓለ ፍልሰታን በማሰብ፣ በይቅርታ፣ በምሕረት፣ በጸሎት፣ በአምልኮት፣ በስግደት፣ ቅዱስ ቊርባንን በመቀበል፣ የምንጾመው ጾም ዋና ዐላማው ከእግዚአብሔር ጋር ለመገናኘት ነው፤ ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ጋር ግንኑነት ሲኖረን የሚጐድለን ነገር እንደሌለ እናውቃለንና፤ ቅዱሳን ሐዋርያት በዚህ ወቅት ጾመው እግዚአብሔርንም ቅድስት ድንግል ማርያምንም አግኝተዋል፤ እኛም እግዚአብሔርንም ቅድስት ድንግል ማርያምንም ለማግኘት እንጾማለን እናገኛቸውማለን ለዚህም ምስክራችን ግዙፉ ንጻሬ ዐይን ሳይሆን ረቂቁ ንጻሬ መንፈስ ነው፤ ፈጣሪዋን የምትከተል መንፈስ ምን ጊዜም ነፃና ደስተኛ ናት፤ ስለዚህ ይህንን ጾም ወጣት ሽማግሌ፣ ሕፃን ዐዋቂ ሳይባል ሁሉም እግዚአብሔርንና ቅድስት ድንግል ማርያምን በመሻት ፍቅርንና መታዘዝን፣ ሰላምንና አንድነትን እንደ ሸማ በመጎናጸፍ ሁሉም ሊጾመው ይገባል፡፡ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ እየታየ ያለው ተስፋ ሰጭ የሆነ የሀገራችን ሰላምና የመግባባት መንፈስ ሥር እንዲሰድ አጥብቀን ወደ ፈጣሪ የምንጮኽበት ጾም ሊሆን ይገባል፡፡ በተለይም በሰው ሠራሽ ምክንያቶች ከቀያቸው የተፈናቀሉና ጕዳት የደረሰባቸው ወገኖችን እንደዚሁም በሌላ ምክንያት የኑሮ እጥረት ያጠቃቸው ድሆችን ካለን ከፍለን በመመገብና በማልበስ ለእግዚአብሔር እንታዘዝ፤ ለወገኖቻችንም እንድረስ ፡፡

የዘንድሮ የጾመ ማርያም ሱባዔን ልዩ የሚያደርገው ለረጅም ጊዜ ተለያይተው የቆዩ የቤተ ክርስቲያናችን አባቶች መከፋፈሉ ቀርቶ በሰላምና በአንድነት ሆነው ሃይማኖታቸውን ሕዝባቸውንና ሀገራቸውን ለማገልገል በተስማሙበት ማግስት፣ እንደዚሁም ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ በአንድነት የነበሩትና ተለያይተው የማያውቁት የኢትዮጵያና የኤርትራ ሕዝቦች በሰላም ለሰላም ተባብረው ለመኖር ቃል በገቡበት ታሪካዊ ወቅት ላይ የሚጾም ጾም መሆኑ ነው፤ ይህ ለሕዝባችን ለሀገራችን ለሃይማኖታችን የተሰጠ ታላቅ አምላካዊ በረከት ነው፤ ይህ የሰላም የፍቅርና የአንድነት በረከት በከፍተኛ ጥንቃቄ ልንጠብቀው ይገባናል፤ ከእንግዲህ ወዲህ የሚፈናቀል ሕይወቱንም ሆነ ንብረቱን የሚያጣ ሰው እንዳይኖር፣ ያለፈው ይብቃ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ተወልዶ ያደገባትና እናት ሀገሬ ናት ብሎ የሚኮራባት ኢትዮጵያ የሥጋት አገር እንዳትሆንበት አጥብቀን እንሥራ፣ እንጸልይ፣ እናስተምር ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከሰላም፣ ከፍቅር፣ ከአንድነት፣ ይቅር ይቅር ከመባባል የተሻለ አጀንዳ እንደሌለ ዐውቆ ሰላም የየቀኑ ሳይሆን የየሰዓቱ አጀንዳ አድርጎ እንዲሠራ ከአደራ ጋር መንፈሳዊና አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

መልካም ጾም ያድርግልን እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32018-08-07 13:38:032025-01-28 13:40:32ነሐሴ 1 ቀን 2010 ዓ.ም. የጾመ ፍልሰታ ሙሉ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ሐምሌ 30 ቀን 2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በጅጅጋ፣ በጎዴ ከተማና በሌሎችም ከተሞች በደረሰው አሠቃቂ ግድያና ዘረፋ እንዲቆም ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሰጥተዋል Link to: ሐምሌ 30 ቀን 2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በጅጅጋ፣ በጎዴ ከተማና በሌሎችም ከተሞች በደረሰው አሠቃቂ ግድያና ዘረፋ እንዲቆም ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሰጥተዋል ሐምሌ 30 ቀን 2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ... Link to: ነሐሴ 11 ቀን 2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ሶማሌ፣ በባሌ፣ በሻሸመኔ፣ በጣና በለስና በሌሎችም አካባቢዎች ተፈጽሞአል በተባለውን የሰው መግደልና መፈናቀል እንዲቆም ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሰጥተዋል Link to: ነሐሴ 11 ቀን 2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ሶማሌ፣ በባሌ፣ በሻሸመኔ፣ በጣና በለስና በሌሎችም አካባቢዎች ተፈጽሞአል በተባለውን የሰው መግደልና መፈናቀል እንዲቆም ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሰጥተዋል ነሐሴ 11 ቀን 2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top