• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ጥር 11 ቀን 2014 ዓ.ም የጥምቀት በዓልን በማስመልከት በጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት በተወካያቸው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል።

ጥር 11 ቀን 2014 ዓ.ም የጥምቀት በዓልን በማስመልከት በጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት በተወካያቸው በብፁዕ ዶ/ር አቡነ አረጋዊ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የውጭ ጉዳይና የቅዱስ ፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት የበላይ ኀላፊ ሊቀ ጳጳስ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

ብፁዕ አቡነ ያሬድ የመንበረ ፓትርያርክ ዋና ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ፣የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኀላፊና የአርሲና ምሥራቅ ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የሲዳማ፣ የጌድኦ የአማሮና የቡርጂ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣
ክቡራን ሚኒስትሮች፣
የተከበራችሁ የመንግሥት ልዩ ልዩ ባለ ሥልጣናት፣
ክቡራን አምባሳደሮችና ኮር ዲፕሎማቶች፣
ክቡራን የቤተ ክርስቲያናችን የየመምሪያውና የድርጅት ኀላፊዎች፣
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ኀላፊዎች፣የተከበራችሁ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣
የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ወጣት የሰንበት ት/ቤት ልጆቻችን፣
የተወደዳችሁ የፓሊስና የፀጥታ አካላት፣
በአጠቃላይ በዚህ ታላቅ የጥምቀተ ክርስቶስ በዓል የተገኛችሁ ምእመናንና ምእመናት በሙሉ፤

በንስሓ መንፈስ ወደ እርሱ የሚቀርቡትን በማየ ጥምቀት በማንጻት ከፍዳ ኀጢአት ነፃ የሚያደርግ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ አራት ዓመተ ምሕረት በዓለ ጥምቀት በሰላም አደረሳችሁ።

“ነስሑ እስመ ቀርበት መንግሥተ ሰማያት
መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሓ ግቡ፤”
(ማቴ. 3÷1)፤

ይህንን ቃለ ቅዱስ ወንጌል፣ አጥማቂው ቅዱስ ዮሐንስና ተጠማቂው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትምህርታቸው ርእስ አድርገው ያስተማሩበት ቃለ ብሥራት ነው፡፡ ትምህርቱ የመንግሥተ ሰማያት መግቢያ በር ንስሓ እንደሆነ በዋናነት ያመለክታል፡፡ መንግሥተ ሰማያት ማለት በሰማያትም በምድርም በአጠቃላይ በትዕይንተ ዓለማት ሁሉ በምልአት የምትገኝ የእግዚአብሔር ሥልጣን ናት፤ ጌታችንም ሆነ ቅዱስ ዮሐንስ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሓ ግቡ” የሚለውን አረፍተ ነገር የትምህርታቸው ዋና ርእስ አድርገው ማስተማራቸው፣ የእግዚአብሔር ሥልጣን በተነሳሕያንንና በኢተነሣሕያን ላይ ለይታ ልትፈርድ መዘጋጀቷን ለማመልከት እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ይህንን ግልጽ ሲያደርግ “እነሆ ምሣር በዛፎች ላይ ተቀምጦአል፤ መልካም ፍሬ የማያፈራው ሁሉ ይቈረጣል፤ ወደ እሳትም ይጣላል” ካለ በኋላ “እንግዲህ ለንስሓ የሚገባ ፍሬ አድርጉ” በማለት የንስሓን አስፈላጊነት ያስገነዝባል፡፡ ይህ የንስሓ ጥሪ ለተወሰኑ ሰዎች ሳይሆን ለመላው የሰው ዘር የተላለፈ አምላካዊ ጥሪ ነው፡፡ ምክንያቱም የሰው ዘር በአጠቃላይ በኀጢአት አረም የተዋጠ ሆኖ ስለተገኘ፣ ከዚህ አረም ነፃ ለመሆን በእግዚአብሔር ፊት የመጀመሪያው ተግባር ንስሓ መግባት ስለሆነ ነው፡፡ የትምህርቱ ዋና ዐላማ ሰዎች አምነውና በንስሓ ተራምደው ወደ ጥምቀት ሲደርሱ የእግዚአብሔር ሥልጣን ልትቀበላቸው ዝግጁ ናት የሚለውን መልእክት በዋናነት ማስተላለፍ ነው፡፡ ጌታችን ሲጠመቅ ሰማይ መከፈቱ ይህንን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ሥልጣን በንስሓ ታድሰው ለሚቀርቡና ለሚጠመቁ ምእመናን ያዘጋጀችው ሰማያዊ ርስት ማደልን ብቻ ሳይሆን፣ የእግዚአብሔር ልጅ የመሆን መብትንም ጭምር ለመስጠት ነው፡፡ “ይህ ልጄ ነው” የሚለው አምላካዊ ድምጽም ይህንን ያመሠጥራል፡፡ “ለተቀበሉት ሁሉ ግን የእግዚአብሔር ልጅ የመሆን ሥልጣንን ሰጣቸው” ተብሎ ተነግሮናልና፡፡

የተወደዳችሁ የበዓሉ ተሳታፊዎች ምእመናንና ምእመናት፤

የበዓለ ጥምቀት ዐቢይ ጥሪ፣ ሰማያዊ ርስትንና የእግዚአብሔር ልጅ የመሆን መብትን ለማግኘት በእምነት ገብታችሁ፣ በንስሓ ተራምዳችሁ በጥምቀት ሀብተ ንጽሐን ተጐናጸፉ የሚል ነው፡፡ እዚህ ላይ እኛ ልንወስደው የሚገባን ትልቅ ኀላፊነት እንዴት ንስሓ እንግባ? የሚለውን ነው፡፡ ትምህርቱን በትክክል ተቀብለን ለተግባራዊነቱ በቈራጥነት ከተነሣን፣ ንስሓ መግባት የሚያስፈልገን መሆኑን ለማወቅ የማያወላውል ዘዴ አለን፡፡ እርሱም “ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትፈልጉትን ሁሉ እናንተም እንዲሁ አድርጉላቸው” የሚል ነው፡፡ ይህ ትምህርት ጌታችን ያስተማረው፣ ዓለም በሙሉ “ወርቃማ ሕግ” ብሎ የተቀበለው ነው፡፡ ከዚህ የበለጠ የኀጢአትና የጽድቅ መመዘኛ የሚሆን ሚዛን የለም፡፡ ይህንን ሚዛን በቀጥታ ወደ ራሳችን አእምሮ አስገብተን ከመዘን፣ በአኛ ላይ ሊደረግብን የማንፈልገውን በሌላ ወንድም ላይ እንዳደረግን፣ አእምሮአችን በዝርዝር ይነግረናል፡፡ በዚህ ጊዜ አእምሮአችን የመሰከረብንን ጥፋት ተቀብለን መጸጸትና ንስሓ መግባት ከአኛ ይጠበቃል፡፡ ከዚህ አንጻር አእምሮውን ጠይቆ ከኀጢአት ንጹሕ ነህ የተባለ እዚህ መካከላችን ይኖር ይሆን? የሚለውን ብንጠይቅ ፍጹም ንጹሕ ሆኖ የሚገኝ ያለ አይመስለንም፡፡ ከተገኘም ቅዱስ መጽሐፍ አይቀበለውም፡፡ ለምን ቢባል? ለአንዲት ሰዓት ስንኳ ከስሕተት የማንነፃ ድኩማን ስለሆንን ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ በመልእክቱ ይህንን በተመለከተ ሲያስተምረን ”አልበደልንም የምንል ከሆነ እግዚአብሔርን ውሸተኛ እናደርገዋለን፡፡ ቃሉም በኛ ውስጥ የለም”ይላል፡፡ እንግዲያውስ ሁላችንም በድለናል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔርም፣ አእምሮአችንም በዚህ ተስማምተው አዎን ነው መልሳቸው፡፡ ይህ ከሆነ ዘንድ ሁላችንም ንስሓ መግባት ግዴታችን ነው።

የተከበራችሁ የበዓሉ ተሳታፊዎች ምእመናንና ምእመናት!ንስሓ በሰውና በእግዚአብሔር፣ በሰውና በሰው መካከል እውነተኛ ሰላምንና ዘላቂ ፍቅርን የሚገነባ  የሕሊና መሐንዲስ ነው፡፡ ሰላምና ፍቅር ከሰው ልጆች እየራቀ የመጣው በንስሓ የታጀበ እምነት መከተል ባለመቻላችን እንደሆነ ንጹሕ ልቡና ላለው ሁሉ የተደበቀ ምሥጢር አይደለም፡፡ ከዚህ አኳያ በሀገራችን ውስጥ ላለው ወቅታዊ ሁኔታም ፈውሱ በንስሓ የታጀበ፣ ከእግዚአብሔርና ከሰው ጋር የሚያስታርቅ ሃይማኖትን ገንዘብ አድርጎ መመላለስ የግድ ሆኖ ይገኛል፡፡ ትክክለኛ ንስሓ በራስ ላይ እንጂ በሌላ ላይ መፍረድን አይፈቅድም፡፡ ሁሉም ራሱን ፈትሾ በራሱ ላይ መፍረድ ከጀመረ፣ ያኔ ያማረ ውጤት ይገኛል፡፡ ወደ ፍጹም ሰላም የሚያደርስ መንገድ ያኔ ወለል ብሎ ይታያል፡፡ ስለዚህ ክርስቲያኖች በሕይወት ዘመናችን ሁሉ በራሳችን ላይ እየፈረድንና በንስሓ እየታደስን ልንኖር የሃይማኖታችን መርሕ እንደሚያስገድድ ተገንዝበን ንስሓ በመግባት ወደ ሰከነ አእምሮአችን ልንመለስ ይገባል።

በመጨረሻም ከበዓለ ጥምቀት አስተምህሮ እንዳስተዋልነው፣ በአበው ብሂልም “መተው ነገሬን ከተተው” እንደሚባለው በንስሓ መንፈስ ቅራኔን፣ ጥላቻን፣ በቀልንንና ቂምን እርግፍ አድርገን በመተው ለሰላም የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ ለሀገራችን አንድነትና ለሕዝባችን ደኅንነት የሚበጀውን ሥራ እንድንሠራ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን መንፈሳዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

በዓሉን የደስታ፣ ዘመኑም የሰላም ያድርግልን፤
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ይቀድስ፤
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን።

 

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32022-01-19 14:19:102025-01-28 14:20:07ጥር 11 ቀን 2014 ዓ.ም የጥምቀት በዓልን በማስመልከት በጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት በተወካያቸው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል።
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ታኅሣሥ 29 ቀን 2014 ዓ.ም የልደት በዓልን መግባት አስመልክተው ያስተላለፉት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ታኅሣሥ 29 ቀን 2014 ዓ.ም የልደት በዓልን መግባት አስመልክተው ያስተላለፉት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ታኅሣሥ 29 ቀን 2014 ዓ.ም የልደት በዓልን መግባት አስመልክተው... Link to: የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል Link to: የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top