• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ታኅሣሥ 29 ቀን 2013 ዓ.ም የልደት በዓልን መግባት አስመልክተው ያስተላለፉት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
በሕመም ምክንያት በየጸበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት ሁሉ፤
ከጥንት ጀምሮ የነገረንን ተስፋውን ለመፈጸም በዚህ ዓለም የተወለደው የተስፋ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።

“ወናሁ ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ወትሰምዮ ስሞ አማኑኤል ዘበትርጓሜሁ እግዚአብሔር ምስሌነ፣ እነሆ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች፤ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋራ ማለት ነው” (ኢሳ. 7፥14፤ ማቴ. 1፥23)

የምሕረት አባት እግዚአብሔር አምላካችን በእውነተኛ ዳኝነቱ በኀጢአት ላይ መፍረዱ የማይቀር ቢሆንም ከዚህ ጎን ለጎን ይቅርባይነቱ አይለይም፡፡ በመሆኑም ሰው በበደሉ ምክንያት ቢፈረድበትም የሚድንበትንም ተስፋ ወዲያውኑ ተነግሮታል፤ ሰውም ያንን ተስፋ እንደሚፈጸምለት በማመን ለዘመናት ሲጠባበቅ ኖሮአል፣ ከዚህ አኳያ የተሰጠው ተስፋ በተለያየ ጊዜ፣ በተለያየ አገላለጽ፣ በተለያዩ ቅዱሳን ነቢያት በየጊዜው ተደጋግሞ ሲነገር ቆይቷል፡፡ ከነዚህም መካከል ነቢዩ ኢሳይያስ የተናገረው ትንቢት ይገኝበታል፣ ነቢዩ ስለዚህ ተስፋ ሲናገር “እነሆ ድንግል ትፀንሳለች፣ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች፣ ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች፤ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው” በማለት ተስፋውን በትንቢቱ አጒልቶ ተናግሮአል፡፡ ወንጌላዊ ቅዱስ ማቴዎስም ይህ ተስፋ የተነገረው ለእመቤታችን እናትነት፣ ለጌታችን ልጅነት እንደዚሁም ድኅነትን ለሚሻ ለሰው ልጅ ሁሉ እንደሆነ በወንጌሉ አስረድቶናል፤ በተስፋው መሠረት የሚወለደው ልጅም አማኑኤል የሚል ስም እንዳለውና ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት እንደሆነ በግልጽ ተቀምጦአል፣ ምሥጢሩ ከሕፃኑ መወለድ በፊት በሰውና በእግዚአብሔር መካከል መለያየት እንደነበረ፣ ሕፃኑ አማኑኤል ሲወለድ ግን እግዚአብሔርና ሰው መለያየታቸው ቀርቶ በከዊን አንድ እንደሆኑ ያስረዳናል፤ እንደዚህ ባለ ሁኔታ፣ በትንቢት ሲነገር የቆየው የእግዚአብሔርና የሰው ምሥጢረ ተዋሕዶ በዕለተ ፅንስ በማሕፀነ ማርያም እውን ሆነ፤ ከዚያች ቅጽበት ጀምሮ “አምላክ ሰው ሆነ፤ ሰውም አምላክ ሆነ” ከዘጠኝ ወር በኋላም በዛሬው ዕለት ታኅሣስ ፳፱ ቀን በቤተ ልሔም ከተማ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ፡፡ የእግዚአብሔር ቃል የሰውን ሥጋ ለብሶ ወይም ተዋሕዶ መታየቱ ሰውን እንደታረቀው እና እንዳቀረበው፣ የአካሉ አካል እስከ ማድረግ ድረስ ደርሶም እንደወደደው በግልጽ ታወቀ፡፡ በመሆኑም ይህንን የአምላክና የሰው በከዊን መዋሐድ ያዩ ሰማያውያን ሠራዊት በከፍተኛ አድናቆትና በሐሤት “በሰማያት ለእግዚአብሔር ክብር ይገባል፤ በምድርም ለሰው ልጅ ሰላም ይገባል፤ ምክንያቱም ሰውን በእጅጉ ወዶታልና” በሚል ሰማያዊ አዲስ መዝሙር ቤተ ልሔምን አሸበረቋት፡፡ በቤተ ልሔም የነበሩ እረኞችም የምስጋናውና የክብሩ ተሳታፊዎች ነበሩ፣ ስለዚህ በዓለ ልደተ ክርስቶስ የከዊን ተዋሕዶው በአምላክና በሰው መካከል፣ የአንድነቱ ጥምረት በመላእክትና በሰዎች መካከል የተከናወነበት ታላቅ ቀን በመሆኑ በሰው ልጅ የድኅነት ጒዞ ዋናው መሠረት የተጣለበት ቀን ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር” የተባለው ትንቢትም በዚህ ቀን በትክክል መፈጸሙን እንገነዘባለን፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት፤

ልደተ ክርስቶስ የተለያዩት የተገናኙበት፣ የተራራቁት የተቀራረቡበት፣ ሰማያውያንና ምድራውያን ስለ እግዚአብሔር ክብርና ስለ ሰላም በኅብረት የዘመሩበት ታላቅ በዓል ነው፣ ስለ እግዚአብሔር ክብርና ስለሰላም አስፈላጊነት በተመለከተ ከልደተ ክርስቶስ የበለጠ አስተማሪና ትምህርት ይኖራል ተብሎ አይታሰብም፣ ስለአንድነት ጠቀሜታም ከልደተ ክርስቶስ የተሻለ አስተምህሮ ይኖራል ተብሎ አይታመንም፡፡ ሕዝበ ክርስቲያኑም ሆነ ሌላው ማኅበረሰብ ለሰማያዊም ሆነ ለምድራዊ ኑሮአችን፣ ለነፍሳችንም ሆነ ለሥጋዊ ሕይወታችን የሚበጀን ምንድን ነው? ብሎ የሚጠይቅ ካለ መልሱ ከልደተ ክርስቶስ ይገኛል፤ መልሱ ከሁሉ በፊት ከእግዚአብሔር ጋር መሆን ነው፣ መልሱ ከእግዚአብሔር ሠራዊት ጋር በአንድነት ስለ ሰላም፣ ስለዕርቅና ስለፍቅር መዘመር ነው፣ ይህ ከሆነ የተመሰቃቀለ ሕይወት አይኖርም፤ ሥጋት፣ ጭንቀት አይኖርም፤ ቢከሠትም እንኳ በፍቅርና በሰላም ይሸነፋል፤ ስለዚህ የሰው ልጅ በአጠቃላይ ለሰላምና ለአንድነት ዋጋ እንዲሰጥ ያስፈልጋል፤ ችግሮች በዓለማችን ተበራክተዋል፤ የኮሮና በሽታ በአንድ ወገን ክትባት ተገኘለት ሲባል፣ እንደገና ሌላ መሰል በሽታ በአዲስ ሁኔታ እንደተከሠተ እየሰማን ነው፤ የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታም ገና ፋይሉ አልተዘጋም፣ አለመግባባቶችም እየተካረሩ መጥተው ወደ ግጭት አምርተዋል፣ ረኃብ መፈናቀል እና ሌሎች ችግሮች ዓለማችንን እየናጧት ይገኛሉ፣ ይኼ ለምን ሆነ ቢባል የልደተ ክርስቶስ መልእክት ቸል ከመባሉ የተከሠተ ችግር ከመሆን አያልፍም፡፡ ስለሆነም የዚህ ሁሉ መፍትሔ የሚገኘው ከክርስቶስ ልደት ነውና ልደቱን ስናከብር ለእግዚአብሔር ክብር በመቆም፣ ለሰው ልጅም ሰላምን ለመስጠትና ለመቀበል በመዘጋጀት ሊሆን ይገባል፤ ከዚህም ጋር የታመሙትንና፣ የታሠሩትን በመጠየቅ፣ የተራቡትንና የተጠሙትን በማብላትና በማጠጣት፣ የታረዙትን በማልበስ ለእግዚአብሔር ያለንን ክብርና፣ ለወገን ያለንን ፍቅር በመግለጽ በዓሉን ልናከብር ይገባል፡፡

በመጨረሻም በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ በየአቅጣጫው እየተከሠተ ያለው አለመግባባት ልማታችንን፣ ነፃነታችንንና ሉዓላዊነታችንን የሚፈታተን እንዳይሆን መላው ሕዝባችን በንቃት በጥበብና በማስተዋል እንዲከታተለው፣ ሁሉም ለሀገሩና ለሃይማኖቱ ለወገኑም ተገቢ ትኲረት በመስጠት በጸሎትና በሚችለው ሁሉ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል በዚህ አጋጣሚ አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡ መልካም የልደት በዓል!

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ፤
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32021-01-07 14:09:242025-01-28 14:10:04ታኅሣሥ 29 ቀን 2013 ዓ.ም የልደት በዓልን መግባት አስመልክተው ያስተላለፉት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 23 ቀን 2013 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ Link to: ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 23 ቀን 2013 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 23 ቀን 2013 ዓ.ም የተካሄደው... Link to: ጥር 11 ቀን 2013 ዓ.ም.የጥምቀት በዓልን በማስመልከት በጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ያስተለለፉት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥር 11 ቀን 2013 ዓ.ም.የጥምቀት በዓልን በማስመልከት በጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ያስተለለፉት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥር 11 ቀን 2013 ዓ.ም.የጥምቀት በዓልን በማስመልከት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top