• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

በቅዱስነታቸው ዘመነ ፓትርያርክነት የተላለፉ በታሪክ የሚዘከሩ መመሪያዎች፤

ሀ. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መሪ ዕቅድ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በእግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ በፓትርያርክነት ተሹመው ርእሰ መንበርነቱን እንደያዙ ባስተላፉት የመጀመርያው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የመክፈቻ አባታዊ መልእክታቸው ቤተ ክርስቲያንዋ እንደተቋም ከማእከል ጀምሮ በደረጃ እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ድረስ የሚወርድ ዘመናዊና የተጠና መሪ ዕቅድ ሊኖራት ይገባል የሚል ነበረ፡፡ በዚህ የቅዱስነታቸው ገዢ ሐሳብ ቅዱስ ሲኖዶሱም በመስማማቱ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሊቃነ ጳጳሳት የሚገኙበት ኮሚቴ ተሰይሞ አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያንዋ ሁለንተናዊ ችግሮች በሚገባ እንዲጠና ያደረጉ ሲሆን እነሆ በአሁኑ ጊዜ የቅዱነታቸው ሐሳብ ተቀባይነት አግኝቶና ፍሬ አፍርቶ የመሪ ዕቅድ መምሪያ ተከፍቶና በጽ/ቤት ደረጃ ተዋቅሮ ሥራውን በማከናወን ላይ ነው፡፡ ይህ ከማእከል ጀምሮ ቤተ ክርስቲያንዋን የሚመጥን መሪ ዕቅድ ሊኖራት ይገባል የሚል ሐሳብም ሆነ በጽ/ቤት ደረጃ እንዲቋቋም የተደረገው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዘመነ ፕትርክና በመሆኑ ቅዱስነታቸው በተቋም ደረጃ ለመልካም አስተዳደር መስፈንና ለግልጽነትና ተጠያቂነት አሠራር ሥርዐት መዘርጋት ያላቸውን ምጡቅ ራእይ በተግባር ያረጋገጠ ውጤታማ የሥራ አፈጻጸም ነው፡፡

ለ. የሀብትና ንብረት አያያዝና ቍጥጥርን በተመለከተ፣

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሥልጣነ ፓትርያርክነቱን በያዙ ማግሥት የሰጡት መመሪያ ቢኖር የቤተ ክርስቲያንዋ ሀብትና ንብረት በአግባቡና ዘመኑ በሚፈቅደው መልኩ መያዝ አለበት፣ ሀብት ንብረት ከብክነት ነጻ በሆነ መንገድ በዘመናዊ አሠራር መመራት አለበት፣ ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጀምሮ እስከ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ድረስ ያለው የሒሳብ አሠራር ፈቃድ ባላቸው በውጭ ኦዲተሮች ጭምር በየዓመቱ መመርመር አለባቸው የሚል ሐሳብ ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ በማቅረብ ቢያንስ በማእከል ደረጃ ተግባራዊ እንዲሆን አድርገዋል፡፡ ከዚህ በመነሣትም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሒሳብ በየዓመቱ በውጭ ኦዲተሮች እንዲመረመርና ሥራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል የተደረገው በቅዱስነታቸው ከፍተኛ ጥረት በመሆኑ ሌላው የሥራቸው ውጤትነው፡፡

ሐ. የሒሳብ አያያዝና የሥነ ምግባር መስፈን በተመለከተ፣

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመጀመርያው የሲኖዶስ መክፈቻ ንግግራቸው በአጽንዖት ካቀረቡት መሪ ሐሳብ አንዱ ቤተ ክርስቲያንዋ ከማእከል እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ድረስ ከሙስና መላቀቅና ፍትሓዊ አሠራር መስፈን አለባት የሚል ነው፡፡ በመሆኑም ችግሩ የቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይሆን የሀገራችን ብሎም የመላው ዓለም ችግር በመሆኑ ይህንን የጥፋት መንገድ (ሙስና) በቤተ ክርስቲያን ደረጃ በስፋት የሚስተዋል ችግር መሆኑን በመግለጽ ቤተ ክርስቲያን ወደቀደመ ልዕልናዋ መመለስ ትችል ዘንድ ግብረ ሙስናን የሚፀየፍ መዋቅር መዘርጋት እንዳለበት አመልክተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በተለያዩ ጊዜያት በግልጽ በአደባባይ ወጥተው፣ በዐበይት ጉባኤያት፣ በየዐውደ ምሕረቱ… በማስተማር ሁሉም ሕዝበ ክርስቲያን ሙስናን እንዲፀየፍ በተደጋጋሚ አስተምረዋል፡፡ መመሪያም ሰጥተዋል፡፡

የቤተ ክርስቲያናችን ጠንቅ የሆነው የጥፋት መንገድ (ሙስና) ከቤተ ክርስቲያናችን በዚህ ቅጽበት ይጠፋል ባይባልም ቅሉ የፀረ ሙስና ትግሉን በይፋ፣ በአዋጅና፣ በመመሪያ ደረጃ በተደጋጋሚ በማስተላለፍ ቅዱስነታቸው ለሥነ ምግባር መጠበቅ፣ ለቤተ ክርስቲያን አሠራር ግልጽነትና ተጠያቂነት መስፈን፣ ያላቸውን ጠንካራ አቋም አሳይተዋል፡፡ የሒሳብ አሠራሩም ከነጠላ የሒሳብ አያያዝ (ሲንግል ኢንትሪ) ወደ ሁለትዮሽ የሒብ አያያዝ (ደብል ኢንትሪ) እንዲለወጥ አድርገዋል፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/005-3-1000.jpg 664 1000 tc https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc2024-12-05 10:50:022024-12-05 10:57:50በቅዱስነታቸው ዘመነ ፓትርያርክነት የተላለፉ በታሪክ የሚዘከሩ መመሪያዎች፤
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ... Link to: በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤ Link to: በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤ በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top