• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

መጋቢት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. የዐብይ ጾም መግቢያ ቃለ ምዕዳንና ቡራክ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣
በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፣

እንኳን ለጌታችን፣ ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የ2ዐዐ5 ዓ.ም. መዋዕለ ጾም በሰላም አደረሳችሁ፡፡

“እብለክሙ በመንፈስ ሑሩ፤ ወፍትወተ ሥጋክሙ ኢትግበሩ
በመንፈስ ተመላለሱ እንጂ የሥጋችሁን ምኞት ከቶ አትፈጽሙ እላችኋለሁ”
(ገላ. 5፣16)

የሰው ልጅ ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ ከሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ የተገኘ ፍጡር እንደመሆኑ በሥጋዊ ፍላጎቱ ሳይሸነፍ ራሱን ለመንፈሳዊ ሕይወቱ ማስገዛት እንዳለበት መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳናል፡፡ ከዚህም አንጻር በመንፈስ ተመላለሱ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ፤ ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በሥጋ ላይ ይመኛልና ይላል የእግዚአብሔር ቃል፡፡ ለእግዚአብሔር ሕግ መገዛት እስከተቻለ ድረስ ክፉዉንና በጎውን ለይቶ ማወቅ ስለማያዳግት በተቻለ መጠን በፊታችን ሰኞ መጋቢት 2 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም. በሚጀመረው በታላቁ ጾማችን በዐቢይ ጾም ወራት ጎጂ ከሆኑ ተግባራት ሁሉ መራቅ አለብን፤ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን የማዳን ሥራ ከመጀመሩ በፊት አርባ ቀንና አርባ ሌሊት በመጾም ድኅነተ ነፍስ እንዳስገኘልን ሁሉ እኛም ፈለጉን ተከትለን ጾም በመጾም ጥንካሬን አግኝተን ረቂቅ የሆነውን የዲያብሎስ ፈተና ማሸነፍ በሚያስችለን ቀጥተኛ መንገድ ለመጓዝ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡ ከዚህ አንጻር ለሥጋዊው አካላችን ጥንካሬ፣ ምግበ ሥጋ እንደሚያስፈልገው ሁሉ መንፈሳዊው ሕይወታችንም እንዲጠነክር መንፈሳዊ ምግብ ያስፈልገዋል፡፡ ከጥንት ጀምሮ ወደ እግዚአብሔር ቅርበት የነበራቸው ቅዱሳን አበው በተሞክሮአቸው እንዳስተማሩንና ቅዱሳት መጻሕፍትም እንዳስረዱን መንፈሳዊ አካላችን የሚጠነክረው የሥጋዊ አካላችን ፍላጎት በጾም ኀይል እንዲደክም ስናደርግ ነው፡፡

ሰይጣንና ክፉ ተግባሩ በሰው ላይ ኀይል የሚያገኙበት ምክንያት እኛ ወደ ምግበ ሥጋ ስናዘነብል እንደሆነ በአዳምና በሔዋን የሆነውና በጌታችን ላይ የተቃጣው በምግበ ሥጋ የመፈተን ሙከራ ማስረጃዎቻችን ናቸው፤ የጾም መንፈሳዊ ጥቅም በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን በማያሻማ ሁኔታ ተረጋግጦአል፡፡ ጾም ማለት ቀጥተኛ የቃሉ ትርጒም መተው፣ ወይም እግዚአብሔር ከማይወደው ነገር ሁሉ መራቅ ማለት ነው፤ እንዲህ ከሆነ ከእንስሳትና የእንስሳት ውጤቶችን ጨምሮ ከሌሎች ፍላጎቶች ሁሉ በመራቅ ራሳችንን ተቈጣጥረን በፍጹም አእምሮአችን፣ በፍጹም ልባችን፣ በፍጹም ኀይላችን እግዚአብሔር አምላካችንን ልናመልክና ለእርሱ ፍጹም ታዛዦች መሆን ይጠበቅብናል ፡፡

እንደ ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ሁል ጊዜ ለሀገርና ለኅብረተሰቡ የሚጠቅም መልካም ሥራን ከመሥራት በቀር ጒዳት የሚያደርሱ ተግባራትን ማራመድ ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ በየአቅጣጫው የተዘረጋው የሀገሪቱ የልማት ፕሮጀክት ውጤታማ እንዲሆን እየተደረገ ያለውን ጥረት የምንመለከተው በታላቅ አድናቆት ነው፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጥረቱ አካል በመሆን ጥሪውን ተቀብላ የሚጠበቅባትን ድርሻ ስታበረክት የቈየች ቢሆንም፣ የልማት ፕሮጀክቱ እውን ሆኖ ውጤታማነቱን እስከሚያረጋግጥ ድረስ ብቻ ሳይሆን ቤተ ክርስቲያኒቱ የምታደርገው የተግባር ተሳትፎ ዘወትር ይቀጥላል፡፡ ተግባራችን ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ ሊሆን የሚችለው ርኅራኄን፣ ቸርነትን፣ ምጽዋትን፣ ትዕግሥትን፣ ፍቅርን፣ ስምምነትን፣ ትሕትናን፣ መረዳዳትን፣ መተዛዘንን ገንዘብ አድርገን የጾምን እንደሆነ ነው ፡፡

በጾም ወራት ልንፈጽማቸው የሚገቡን የትሩፋት ሥራዎች ብዙዎች ቢሆኑም በተለይ መሠረታዊ የሆነ የኑሮ ፍላጎት ላልተሟላላቸው ወገኖቻችን ማለትም፣ ልብስ ለሌላቸው ልብስ በማልበስ፤ የምግብ እጥረት ላጋጠማቸው የሚቻለንን በመለገስ፤ ማረፊያ ለሌላቸው መጠለያዎችን በመቀለስ ወገኖቻችንን መርዳት ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የጾም ዋና ዐላማው ለእግዚአብሔር ቃል በሙሉ ኀይላችን በመታዘዝ መዘጋጀት ነውና እግዚአብሔር በቃሉ የነገረንን ሁሉ ከመፈጸም ጋር ሃይማኖታዊና ሀገራዊ ግዴታችንን በመወጣት፣ መንፈሳዊና ማኅበራዊ መርሐ ግብራችንን በማፋጠን፣ መልካም የሆኑትን የልማት ሥራዎቻንን ሁሉ በማከናወን ወርኀ ጾሙን ልናሳልፍ ይገባል፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን መዋዕለ ጾሙን በሰላም እንዳስጀመረን ሱባዔውን በሰላም አስፈጽሞ ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም እንዲያደርሰን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ሕዝባችንን ይባርክ ይቀድስ አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc2013-03-11 10:38:402024-12-04 17:09:56መጋቢት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. የዐብይ ጾም መግቢያ ቃለ ምዕዳንና ቡራክ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ሚያዝያ 27 ቀን 2005 ዓ.ም የበዓለ ትንሣኤ ሐዋርያዊ መልእክት Link to: ሚያዝያ 27 ቀን 2005 ዓ.ም የበዓለ ትንሣኤ ሐዋርያዊ መልእክት ሚያዝያ 27 ቀን 2005 ዓ.ም የበዓለ ትንሣኤ ሐዋርያዊ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top