• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል የቅዱስነታቸው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ

በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን

ብፁዕ ኣቡነ ሳዊሮስ
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ ኣስኪያጅ፤
ብፁዕ ኣቡነ ዲዮስቆሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ፤
ብፁዕ ኣቡነ ሕርያቆስ
የኣዲስ ኣበባ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጳሳት፣
ክቡር…..
ክብርት…..
ክቡራን ሚኒስትሮችና ከፍተኛ የመንግሥት ባለ ሥልጣናት፣
ክቡራን ኣምባሳደሮችና የኮር ዲፕሎማቶች፣
ክቡራን የቤተ ክርስቲያናችን የየመምሪያውና የየድርጅቱ ኃላፊዎች፣
የተከበራችሁ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ ኣገልጋዮችና ሰራተኞች፣
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ጀግኖች ኣርበኞች፣
የተከበራችሁ የፀጥታ ኣስከባሪ ኣባላት፣
የተወደዳችሁ የሰንበት ት/ቤት መዘምራን ልጆቻችን፣
በኣጠቃላይ በዚህ ታላቅ ሥነ በዓል የተገኛችሁና በዓለም ዙሪያ ሆናችሁ በዓሉን በመከታተል የምትገኙ ክርስቲያኖች በሙሉ፦

ስሕተት በወለደው በደልና ኃጢኣት የደከሙትን በኃይለ መስቀሉ የሚታደግ ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት በዓለ መስቀሉ በሰላም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
“ወለእለ ፃመዉ በመስቀሉ ይባልሕ፡- የደከሙትን በመስቀሉ ይታደጋል፤ (መጽሓፈ ኪዳን)፤

እግዚአብሔር ኣምላካችን በሁለመናው እንከን የለሽ ፍጹም ኣምላክ ነው፤ እንደዚህም በመሆኑ ጥፋትን የማይወድ ኣምላክ ነው፤ ይሁንና የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ሕግ ላይ ድፍረትን የተሞላ ስሕተት ወይም ጥፋት በመፈጸሙ እግዚአብሔርን ኣስቈጣ፤ ከዚህ ኣንጻር ሰው በዚህ ተግባሩ ደካማ ሆኖ ተገኘ። እግዚአብሔርም ፈታሒ በጽድቅ፣ ኰናኒ በርትዕ ነውና ሰውን በጥፋቱ ቀጣ፤ የቅጣቱም ዓይነት ሞት ነበረ፤ በሰው ላይ የተላለፈው የሞት ቅጣትም በምድርም፣ በሰማይም ተፈጻሚ ሆነ፤ ይህም ማለት ሰው በምድራዊም ሆነ በሰማያዊ ኑሮው ከእግዚአብሔርና የእግዚአብሔር ከሆነው ሁሉ ተለየ ማለት ነው፤ ይህ ቅጣት ለሰው ልጅ እጅግ የመረረ ቅጣት ነበረ።

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት!
ክቡራን የበዓሉ ተሳታፊዎች!

እግዚአብሔር በዳኝነቱ ፈራጅና ቀጪ እንደ ሆነ ሁሉ፣ በኣባትነቱ ደግሞ መሓሪና ይቅር ባይ ነው፤ በመሆኑም በኃጢኣት ደክሞ የወደቀውን የሰው ልጅ በቤዛዊ ሞቱ ከሞተ ኃጢኣት የሚያድነው መሆኑን የሚያመለክት ተስፋ ሰጠው።
ተስፋውን በነቢያቱ ኣማካኝነት ሲገልጽለት ከቈየ በኋላ፣ ሰውነታችንን ተዋሕዶ በዚህ ዓለም ተገለጸ፤ በዚህ ዓለም ሰው የሚድንበትን መንገድ በቅዱስ ወንጌል ካስተማረና በተግባር ካሳየ በኋላ፣ ቤዛ ሰብእ የሆነው ሞቱን በመስቀል ላይ በመቀበል ቅጣታችንን እንዲነሣ ኣደረገልን፡፡  ቅዱስ መጽሓፍ ይህንን ሲገልጽ፦ “ሁሉም በኣዳም እንደሚሞቱ ሁሉም በክርስቶስ ይድናሉ” ይላል። በስሕተት፣ በበደልና በኃጢኣት የደከመው የሰው ልጅ በክርስቶስ ቤዛዊ ሞት ምክንያት ነጻነትን ኣግኝቶ ወደ ቀደመ ክብሩና ርስቱ ተመለሰ፤ ቤተ ክርስቲያን “የደከሙትን በመስቀሉ ይታደጋል” በማለት የምታስተምረን ይህንን እውነት ለመግለጽ ነው፡፡ ለዚህም ዋና ማስረጃዋ ጌታችን በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሳለ “ዛሬውኑ ከኔ ጋር በገነት ትሆናለህ” በማለት በቀኙ በኩል ለተሰቀለው በደለኛ የገባውና የፈጸመው ቃል ኪዳን ነው፤ ይህም ቃል ኪዳን ለኣማንያን ሁሉ የተገባ ቃል ኪዳን መሆኑ እሙን ነው።

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት!
የተከበራችሁ የበዓሉ ተሳታፊዎች!

ምንም እንኳ በመስቀል ላይ በተፈጸመው የጌታችን ቤዛዊ ሞት ምክንያት ነባሩ ቅጣታችን ወይም ጥንተ ኣብሶ ቢነሣም በገቢር ኣበሳችን ምክንያት ዛሬም ከስሕተት መጽዳት ኣልቻልንም፡፡ በመሆኑም ዛሬም ከእውነት ጋር መጋጨታችን ስለ ቀጠለ በየጊዜው በምንፈጽመው የገቢር ኣበሳ እግዚአብሔርን ማስቈጣታችን ኣልቀረም።  የድኅነታችን ምልክትና ምስክር የሆነው ዕፀ መስቀል በሰዎች እንዲቀበር መደረጉም፣ የገቢር ኣበሳችን መቀጠሉን የሚያመለክት ምስክር ነው፡፡
ሆኖም መስቀልን መደበቅም ሆነ መሰወር ከሰው ዓቅም በላይ ነበረና በእግዚአብሔር ኃይል በጢሰ ዕጣን ኣመልካችነት ከተቀበረበት ጕድጓድ ሊወጣ ችሎኣል፡፡ እነሆም መስቀሉ እስከ ዛሬ ድረስ የእውነት መስካሪና የድኅነት ምልክት ሆኖ ቀጥሎኣል፤ ለወደፊትም በዚህ ይቀጥላል።

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት
ክቡራን የበዓሉ ተሳታፊዎች!

የመስቀሉ ዓበይት መልእክቶች ሰው ሊያምንባቸው፣ ሊቀበላቸውና ሊኖርባቸው፣ በውጤቱም በሥጋውም ሆነ በነፍሱ ሊድንባቸው እንደ ተሰጡ የማንስተው ሓቅ ነው፡፡  ሆኖም ሰዎች በኣንድ ጆሮኣችን ሰምተን በሌላኛው ጆሮኣችን ከመጣል ባለፈ፣ ያመጣነው ለውጥ እንደሌለ ተግባራችን ራሱ ምስክር ነው። ዛሬም ሕገ እግዚአብሔር በድፍረት ይጣሳል፤ የጥሰቱ ውጤትም እንደምናየው ዓለማችንን በኣጠቃላይ በመኖርና ባለመኖር ስጋት ውስጥ እየከተታት ይገኛል፡፡
ታድያ እኛስ በዚህ ሁሉ ኣልደከምንምን? የሚታደገን መስቀላዊ ኃይልስ ኣያስፈልገንምን? ለሰላማችን መጠበቅና ለድኅነታችን ዋስትናስ ከመስቀሉ ቃልና ኃይል የበለጠ ሌላ ኣለን? እንደ እውነቱ ከሆነ በንጹሁ ኣእምሮኣችን በደምብ ካስተዋልነው፣ ከመስቀሉ ቃል የበለጠ ለሰው ልጆች ሰላምንና ድኅንነትን የሚሰጥ ሌላ ኃይል በዓለማችን ውስጥ ኣይገኝም። ስለሆነም ፍጹምና ዘላቂ ሰላምን የምንሻ ከሆነ፣ በመስቀሉ ቃል እንመራ፤ የመስቀሉ ቃል ማለት ይቅርታንና ዕርቅን፣ እኩልነትንና ኣንድነትን፣ ፍትሕንና ርትዕን ማረጋገጥ ማለት እንደሆነም በውል እንወቅ፤ በዚህ ሕይወት መኖር ከጀመርን ድክመታችን በመስቀሉ ተወገደ ማለት ነው።

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት!
ክቡራን የበዓሉ ተሳታፊዎች!

የዘንድሮ በዓለ መስቀል ኣከባበር ልዩ የሚያደርገው፣ እግዚአብሔር የሰጠንን የውሀ ጸጋችን ፍትሓዊ በሆነ መንገድ ለመጠቀም በኣንድነት ተባብረን ባካሄድነው ጥረት፣ የሕዳሴ ግድባችንን ኣጠናቀን ባስመረቅንበት ማግሥት እየተከበረ ያለ መሆኑ ነው፡፡  ይህ ክሥተት ለሃገራችን ዳግም ልደትን ያበሰረ ስኬት ነው ብንል ማጋነን ኣይሆንም፤ በዚህም እግዚአብሔር ኣምላካችንን ማመስገን ይገባናል፤ በስራው ላይ ታሪካዊ ኣሻራቸውን ያሳረፉትንም ሁሉ መመስገን ይገባቸዋል እናመሰግናቸዋለንም። በቀጣይም ሃገራችን ልትሰራቸው በዕቅድ የያዘቻቸውን ታላላቅ የልማት ስራዎች፣ በፍጥነትና በጥራት ተሰርተው ለሕዝባችን ጥቅም እንዲውሉ ሁላችንም መረባረብ ይኖርብናል፤ ታላላቅና ዘመን ተሻጋሪ እንዲሁም ችግር ኣስወጋጅ የሆኑ ስራዎች እውን ሊሆኑ የሚችሉ፣ ሕዝቡ በኣንድነትና በኅብረት ተነሥቶ ወደ ትግበራ ሲገባ እንደሆነ ከታላቁ የሕዳሴ ግድባችን ተምረናል፤ በመሆኑም በሕዳሴ ግድባችን ያሳየነውን ትብብርና ተነሣሽነት፣ ኣሁንም ኣጠናክረን መቀጠል ይገባናል፤ መንግሥትም ከዚህም ከዚያም የሚታዩትን ኣለመግባባቶች በዕርቅና በይቅርታ በማለፍ፣ እኩልነትን፣ ፍትሕንና ርትዕን በማረጋገጥ፣ እንደዚሁም ለሰላም መስፈን ረጅም ጉዞ በመሄድ ሕዝቡን ወደ ኣንድነት የማምጣት ኃላፊነቱን እንዲወጣ በዚህ ኣጋጣሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

በመጨረሻም

የመስቀሉ መልእክት የሰው ልጆችን ሁሉ በሰላም፣ በሕይወት፣ በእኩልነትና በኣንድነት ማኖር መሆኑን ከልብ ተገንዝበን፣ በያዝነው ኣዲስ ዓመት እርስ በርሳችን ከመጠፋፋት ይልቅ በጋራ ሰርተን በጋራ የምንለማበትን ምርጫችን እናድርግ በማለት በእግዚአብሔር ስም ኣባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን። በዓለ መስቀሉን የሰላም በዓል ያድርግልን፤ ለሃገራንና ለዓለሙ ሁሉ ሰላሙን ይስጥልን!

እግዚአብሔር አምላካችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓም
ኣዲስ ኣበባ ኢትዮጵያ።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/2018-meskel.jpg 954 1080 tc https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc2026-02-28 20:13:562026-02-28 20:13:56መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል የቅዱስነታቸው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: መስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም ርዕሰ ዐውደ ዓመት የዘመን መለወጫ በዓል መግባትን አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ Link to: መስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም ርዕሰ ዐውደ ዓመት የዘመን መለወጫ በዓል መግባትን አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ መስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም ርዕሰ ዐውደ ዓመት የዘመን... Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top