• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

መስከረም 1 ቀን 2010 ዓ.ም. የዘመን መለወጫ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
በሕመም ምክንያት በየጸበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤

የዘመናትና የፍጥረታት ፈጣሪ የሆነው እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ ሁለት ሺሕ ዘጠኝ ዓመተ ምሕረት ወደ ዘመነ ማርቆስ ሁለት ሺሕ ዐሥር ዓመተ ምሕረት በሰላም አደረሳችሁ፡፡

“አንሶስዉ እንዘ ብክሙ ብርሃን
ብርሃን ሳለላችሁ በብርሃን ተመላለሱ።”
(ዮሐ. 12፥35)

የብርሃን ጸጋ ለሰው ልጆች ወይም በአጠቃላይ ለፍጥረታት ሁሉ ከተሰጡ የእግዚአብሔር ስጦታዎች ትልቁ ነው፤ ብርሃን የሥራ መሣሪያ ነው፣ ብርሃን የመልካም ነገር ሁሉ ተምሳሌት ነው፤ እግዚአብሔር ራሱ በባሕርዩ ብርሃን ከመሆኑም ሌላ በእርሱ ዘንድ የማይጠፋ ብርሃን እንዳለ በቅዱስ መጽሐፍ ተገልጾአል፤ የሰው ልጅ ከወዲያ ወዲህ፣ ከወዲህ ወዲያ ተንቀሳቅሶ፣ ነግዶ፣ አርሶ፣ ሠርቶ፣ ተምሮና አስተምሮ ለኑሮው የሚያስፈልገውን ሁሉ ለማግኘት ብርሃን የግድ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህም ጋር ሙሉ ጤና፣ ቀና የሆነ አእምሮ፣ ሰላምና ፍቅር ለሰው ልጅ ብልጽግና ወሳኝ ቦታ አላቸው፤ እነዚህ በሰው ልጅ መንፈሳዊና ሥጋዊ ሕይወት ላይ ያላቸው ጸጋ እጅግ የላቀ በመሆኑ በቅዱስ መጽሐፍ አገላለጽ ብርሃን እየተባሉ ይጠቀሳሉ፡፡ እንደዚሁም ዕድሜና መልካም ዘመን በተመሳሳይ አገላለጽ ብርሃን ተብሎ ይመሠጠራል፤ ምክንያቱም ብርሃን በሌለበት ሁኔታ ምንም ሥራ መሥራት እንደማይቻል ሰላማዊ ዘመን ከሌለም ልማትና እድገት ማስመዝገብ አይቻልምና ነው፤ በመሆኑም ዕድሜና ዘመንም ሌላው ታላቁ የእግዚአብሔር ብርሃን ነው፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ብርሃን ሳለላችሁ በብርሃን ተመላለሱ” ሲል የዕድሜና የጊዜ ብርሃንነትን ማመልከቱ እንደሆነ ዐውደ ምንባቡ በግልጽ ያሳያል፤ ምክንያቱም እርሱ በዚህ ዓለም በመምህርነት የተገለጸበት ዘመን ወደ መጠናቀቁ እየተቃረበ በነበረበት ጊዜ የተናገረው ከመሆኑ ጋር ባላችው አጭር የትምህርት ዕድሜ ወይም ዘመን ሰዎች በእርሱ ብርሃንነት እንዲያምኑ የቀሰቀሰበትና ያስተማረበት ትምህርት ነው፡፡ በእርግጥም ላስተዋለውና በሥራ ለተጠቀመበት፣ ጊዜ ታላቁ ብርሃን ነው፤ ጊዜ ሲቀና ነገሩ ሁሉ ብርሃን ይሆናል፤ ጊዜው ከጨለመ ደግሞ ዙሪያው ሁሉ ጨለማ ይሆናል፤ ዕድሜያችን ወይም ዘመናችን በሕይወታችን ውስጥ ለልማትም ሆነ ለጥፋት ለጽድቅም ሆነ ለኀጢአት፣ ለትንሣኤም ሆነ ለውድቀት መሣሪያነቱ የታወቀ ነው፤ ምክንያቱም ሁሉም የሚሠራውና የሚከናወነው በጊዜው ነውና፡፡ በዘመናት ውስጥ ብርሃናውያን የሆኑ ዓመታት እንደነበሩ ሁሉ ጽልመታውያን የሆኑ ዓመታትም በሀገራችንም ሆነ በሌላው ዓለም እንደነበሩ እናውቃለን፡፡ እነዚህ ተቃራኒ የሆኑ ነገሮች በየፊናቸው ለሰው ልጆች ያተረፉት ስጦታም በስማቸው ልክ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ ዘመናትን ብርሃናውያን ወይም ጽልመታውያን እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ የሰው ልጅ ሚና ትልቅ እንደሆነ የማይካድ ነው፡፡

የሰው ልጅ የማስተዋልና የመቻቻል፣ የመታገሥና የመወያየት፣ የፍቅርና የስምምነት፣ የሰላምና የአንድነት ጠቃሚነትን ዘንግቶ፣ በስሜትና በወቅታዊ ትኲሳት፣ እንደዚሁም የእግዚአብሔርን የሰላም ድምፅ አልሰማ ብሎ በራስ ወዳድነትና በስግብግብነት ተሸንፎ ወደ ትርምስ ሲገባ ዘመኑ ጽልመታዊ መሆኑ አይቀሬ ነው፡፡ በሰው ችኩልና ደካማ አስተሳሰብ የተጨናነቀ ጽልመታዊ ዘመን ከውድመትና ከጥፋት በቀር አንዳችም ትርፍ እንደሌለው ከሀገራችን ተሞክሮ የበለጠ መምህር አይኖርም፡፡ በሌላ በኩል ሰዎች ከእርስ በርስ ግጭት ተላቅቀው ሰላምንና ፍቅርን፣ አንድነትንና እኩልነትን፣ መቻቻልንና መስማማትን፣ መወያየትንና መቀራረብን፣ ወንድማማችነትንና መከባበርን ያረጋገጠ፣ ትዕግሥትና አስተዋይነት የማይለየው የእግዚአብሔርን ድምፅ በመከተልና አእምሮን በማስፋት መኖር ሲጀመሩ ዘመኑ ብርሃናዊ እንደሚሆን፣ ልማቱና እድገቱም እንደሚፈጥንና እንደሚረጋገጥ አሁንም በሀገራችን ወቅታዊ ተሞክሮ ተረድተነዋል፤ ይህ ሁሉ እውነታ የሚያሳየው የዘመን ብርሃንነትና ጽልመትነት የሚወሰነው፣ እኛ ሰዎች በምናውጠነጥነው አስተሳሰብና በምናደርገው እንቅስቃሴ እንደሆነ ማስተዋል ተገቢ ነው፤ ለዚህም ነው ኀላፊነቱም ተመልሶ ወደ እኛ የሚመጣው፡፡

ጌታችንም ምርጫውንና ውሳኔውን ለእኛ ትቶ ብርሃን ስላላችሁ በብርሃን ተመላለሱ በማለት ገለጻውንና ትምህርቱን ብቻ መናገሩ ከዚህ የተነሣ እንደሆነ ማስተዋል ይገባል፡፡ ከእነዚህ ከሁለቱ የሚሻለንን መምረጥና መከተል የእኛ ፈንታ ነው፤ ምርጫችን ሰላምና አንድነት ከሆነ ዘመኑ ብርሃን ነው፤ ተቃራኒው ከሆነ ደግሞ የኋልዮሽ ጒዞ ይሆናል፤ ስለሆነም ምርጫችን ሰላምና አንድነት እንዲሆን ሁላችንም ተስማምተን መወሰን አለብን፡፡ ማንም ሰው ብርሃንና ጨለማ ጎን ለጎን ቀርበውለት የትኛውን ትመርጣለህ የሚል ጥያቄ ቢቀርብለት ያለማመንታት ብርሃኑን እንደሚመርጥ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ችግሩ ሰዎች ይህንን ግልጽና ጠቃሚ ምርጫ ተቀብለው ተጠቃሚ እንዳይሆኑ ብዙ የሚያታልሉና በድብብቆሽ የሚመላለሱ አካላት በመካከሉ ይገቡና ጨለማውን ብርሃን፣ ብርሃኑንም ጨለማ አስመስለው ሰውን ወደገደል መክተታቸው ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ብርሃናዊና መልካም የሆነ ምርጫችንን ጥያቄ ውስጥ እንዲገባ ያደርጉታል፤ እኛ ሰዎች አእምሮአችንን በሚገባ መጠቀም ያለብን እዚህ ላይ ነው፤ ማለትም እኛው ራሳችን የሚጠቅመንና የማይጠቅመንን የመለየት ዐቅም ስላለን ዓቅማችንን ተጠቅመን ለዘላቂ ጥቅማችንና ለትክክለኛ ምርጫችን መወገን ይኖርብናል ማለት ነው፡፡

ሰዎች የሆን ሁላችን ባለ አእምሮዎች ሆነን ተፈጥረናል፤ አእምሮ ከእግዚብሔር ጋር የሚያመሳስለን ስለሆነ ከሀብት ሁሉ የበለጠ ሀብት ነው፤ ይህንን አእምሮአችንን ካዳመጥነውና ከተከተልነው ሐቁን አይስትም፤ አመዛዝኖ፣ ገምግሞ ለክቶ፣ ጠቃሚውን ነገር ከልባችን ውስጥ ቊጭ ያደርግልናል፤ ነገር ግን ትዕግሥትን፣ ማገናዘብን፣ ቆም ብሎ ማሰላሰልን፣ ምክንያታዊ መሆንን፣ ማመዛዘንን፣ ፈሪሀ እግዚአብሔርና ፈቃደ እግዚአብሔር መከተልን ይፈልጋልና እነዚህን እንደ ግብአት አድርገን ልናቀርብለት ይገባል፤ ይህንን መጠቀም ስንችል የዘመናችንና የዕድሜያችን ብርሃን ዋስትና ይኖረዋል፤ ጨለማም አያሸንፈውም፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን፤

ለዐሥር ዓመታት ያህል የተጓዝንበት የሦስተኛው ሺሕ ወይም ሚሊኒየም ዐቢይ ዘመን ለኢትየጵያ ሀገራችን ብርሃናዊ ዘመን የፈነጠቀበት ወቅት ነው፤ ምክንያቱም በዚህ ዘመን ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ያልተነካ ሀብታችን እርሱም የዐባይ ወንዝ ሀብታችንን ለመቋደስ የሚያስችል ግዙፍ የልማት ሥራ ተጀምሮ ወደ መጠናቀቅ እየተቃረበ ያለበት እጅግ ብርሃናዊ ዘመን በመሆኑ ነው፡፡ በሠለጠነው የምዕራቡ ዓለም ካልሆነ በቀር በአፍሪከ ምድር ለዚያውም በድርቅ፣ በረኃብና በጦርነት ትታወቅ በነበረችው ኢትዮጵያ ይሆናሉ ተብለው የማይታሰቡ እጅግ ግዙፍ የሆኑና የሕዝባችንን መሠረታዊ የእድገት ለውጥ የሚያረጋግጡ የኮንስትራክሽንና የኢንዱስትሪ፣ የትምህርትና የጤና ተቅዋማት በፍጥነት እየገሠገሡ መገኘት በዚህ ብርሃናዊ ዘመን የዕለት ተዕለት ትእይንት እንደሆኑ በዐይን እየታየ ነው፤ ይህ ጸጋ እንዲሁ ያለ መሥዋዕትነት የተገኘ ሳይሆን እኛ ኢትዮጵያውያን ከሁሉ በላይ ሰላምንና ልማትን መርጠን በአንድነት ወደ ብርሃናዊ አስተሳሰብ ስለገባን ነው፡፡ እግዚአብሔርም በብርሃን ተመላለሱ ያለው ይህንን ለማመልከት ነውና በዚህ ምክንያት ትክክለኛ ምርጫችንን እርሱ ስለባረከልን የልማትና የእድገት ተምሳሌት መሆን እንደቻልን አንሥተውም፡፡ ዛሬም ወደማንወደውና ወደማንመርጠው ጨለማ ሊከቱን የሚሹ እንደ ኤች አይ ቪ ኤድስና ሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር እንደዚሁም በሕዝባችን መካከል መለያየትና መቃቃር ሊያስከትሉ የሚችሉ አፍራሽ ድርጊቶች ብቅ ብቅ በማለት እየተፈታተኑን እንደሆኑ መዘንጋት የለበትም፤ እነዚህ ሁሉ በተግባር ያየናቸው የሕዝባችን ቀንደኛ ፀርና የጨለማ አበጋዞች፣ የልማታችንና የሰላማችን ዕንቅፋቶች ናቸውና ሕዝቡ በተለመደው ሃይማኖታዊና አርቆ ማሰብ ኀይሉ እንዲመክታቸው በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

በመጨረሻም፡ የዛሬ ዐሥር ዓመት “ታላቅ ነበርን ታላቅም እንሆናለን” በማለት ለሦስተኛው ሺሕ ወይም ሚሊኒየም ዐቢይ ክፍለ ዘመን የገባነውን ቃል በማደስ በአዲሱ ዓመት ካለፈው ዓመት በበለጠ ጠንክረን በመሥራት ልማታችንንና እድገታችንን በፍጥነት በማሳደግ፣ የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታን ባለን የተሞክሮ አሠራር በመመከት፣ እንደዚሁም ሕገ ወጥ ዝውውርን፣ ሀገርንና ሕዝብን የሚጎዳ ድርጊትን በማክሸፍ፣ በሃይማኖትና በሰላም መርሕ በመመራት አዲሱን ዘመን ብርሃናዊ እንድናደርገው አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

አዲሱ ዘመን የሰላም የፍቅርና የብልጽግና ያድርግልን፤ እግዚአብሔር አምላካችን ኢትዮጵያንና ሕዝባችንን ይባርክ ይቀድስ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32017-09-11 13:28:552025-01-28 13:30:19መስከረም 1 ቀን 2010 ዓ.ም. የዘመን መለወጫ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ነሐሴ 16 ቀን 2009 ዓ.ም. የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ በዓለ ዕርገት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ነሐሴ 16 ቀን 2009 ዓ.ም. የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ በዓለ ዕርገት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ነሐሴ 16 ቀን 2009 ዓ.ም. የእመቤታችን ቅድስት ድንግል... Link to: መስከረም 16 ቀን 2010 ዓ.ም. የመስቀል ደመራ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: መስከረም 16 ቀን 2010 ዓ.ም. የመስቀል ደመራ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ መስከረም 16 ቀን 2010 ዓ.ም. የመስቀል ደመራ በዓል...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top