• Amharic  
  • English  
  • ቀዳሚ ገጽ
  • የኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
    • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • ልዩ ጽ/ቤት
    • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
    • የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች
    • የሀገር ውስጥ ሐዋርያዊ አገልግሎቶች
    • የውጭ አህጉር ሐዋርያዊ ጒዞ
  • ቃለ በረከት
  • ዜና መዋእል
  • አርዕስተ ሊቃነ ጳጳሳት
  • ያግኙን
  • Menu Menu

ሐምሌ 25 ቀን 2010 ዓ.ም. ለሃያ ሰባት ዓመታት በስደት ይኖሩ የነበሩት የኢትዮጵያ አራተኛ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በዕርቀ ሰላም እና በአንድነት ወደ ሀገራቸው ገብተዋል፡፡

ስድስተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ቦሌ ዓለም ዐቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝተው ቅዱስነታቸውን የተቀበሏቸው ሲሆን በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዐውደ ምሕረት ለአቀባበሉ ለተሰበሰቡት ካህናትና ሕዝበ ክርስቲያን የሚከተለውን ታሪካዊና ሐዋርያዊ የአንድነትና የሰላም ቃለ በረከት አስተላልፈዋል፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

ናሁ ሠናይ ወናሁ አዳም ሶበ ይሄልዉ አኀው ኅቡረ፡፡ (መዝ. 132፥1)

• ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 4ኛ ፓትርያርክ፣
• ከሀገር ውስጥና ከውጭ አህጉር የመጣችሁ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣
• የተወደዳችሁና የተከበራችሁ የዚህ ልዩ የሆነ የቤተ ክርስቲያናችንን ክብረ በዓል ለማክበር በዚህ ዐውደ ምሕረት የተገኛችሁ እንግዶች በሙሉ።

ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ‹‹ናሁ ሠናይ ወናሁ አዳም፤ ሶበ ይሄልዉ አኀው ኅቡረ — ወንድሞች በኅብረት ቢኖሩ፣ እነሆ መልካም ነው፤ እነሆም ያማረ ነው›› ሲል ጸልዮዋል፡፡ እኛም የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክታችንን የምናስተላልፈው በታላቅ መንፈሳዊ ደስታና ኅብረት ነው፡፡

እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ ከብዙ ሺህ ዘመናት ጀምራ በፈጣሪዋ ታምና ነቅዕ በሌለው ሁናቴ በሃይማኖቷ ጸንታ፤ በነፃነቷ ኮርታና ታፍራ ለሥራዋም የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት መሆኑን አስተምራ፤ ጸሎቷንና ልመናዋን ‹‹ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ ኀበ እግዚአብሔር›› ሲል ንጉሥ ዳዊት በመሰከረላት መሠረት ዕለት በዕለት እያስታኮተችና ወደ እግዚአብሔር እየጸለየች የምትኖር ስብሐተ እግዚአብሔር በየጊዜው የማይለይባት ሀገረ እግዚአብሔር ናት፡፡

ከላይ ከፍ ብሎ በመግቢያችን “ሶበ ይሄልዉ አኀው ኅቡረ — ወንድሞች በጋራ ቢኖሩ ቢተዳደሩ መልካም ነው” ሲል ነቢዩ በተነበየው ትንቢትና ባቀረበው ልመና መሠረት ታማኞቹ ለመሆን ለመረጠን ፈጣሪያችን የምንመልሰው ወሮታ ቢኖር የተቀበልነውን አምላካዊ አደራ እኛም ሠርተን ጠብቀን ተከታዮቻችንንም በፍትሕ መንፈሳዊ፣ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በሥርዐታችን፣ በባህላችንና በወጋችን መሠረት እንዲጸኑና እንዲሠሩ በመንፈሳዊ አገልግሎታቸውም በኩል ለቤተ ክርስቲያናችንና ለቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ይህን የመረዳዳትንና በአንድነት የመኖርን ሐሳብ እናስተምራቸዋለን ብለን በፍጹም ልባችን ተነሣሥተናል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ 4ኛው የቤተ ክርስቲያናችን ፓትርያርክ!
ሁሉም እንደሚረዳው እኛም አሜሪካን አገር በነበርንበት ወቅት የቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደራዊና ሲኖዶሳዊው አንድነታችንን ወደቀደመው መሥመሩ ለመመለስ ብዙ ተጒዘን እንደነበር ቅዱስነትዎ ያውቀዋል፡፡

በቤተ ክርስቲያናችን የተፈጠረውን ልዩነትና የአንድነት መታጣት ችግሩ ከታየበት ጊዜ ጀምሮ በየቅዱስ ሲኖዶሱ ጉባኤያት በጸሎት ያልታሰበበትና ያልተወሰነበት ጊዜ የለም፡፡ ሆኖም የሀገራችንንና የቤተ ክርስቲያናችንን የአንድነት ህልውና በሚፈልጉ ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ካህናት ተደጋጋሚ ሙከራ ሲደረግ መቆየቱ የሂደቱ ዋነኛ ታሪክ ነው፡፡

አሁንም ደግሞ ከሁሉ በበለጠ የኤ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ያደረጉት የማቀራረብና የማግባባት ሥራ ከ45 ዓመታት ወዲህ ባለው የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ባልታየ ሁናቴ የቤተ ክርስቲያናችንን አንድነት መንግሥታዊ ድጋፍ ታክሎበት ችግሩ በሚፈታበት ሥፍራ በአካል ጭምር ተገኝተው በሠሩት ሥራ የቤተ ክርስቲያናችን የአንድነት ታሪክ ዋና ባለሟል ያደረጋቸው ስለሆነ ቤተ ክርስቲያናችን በሠሩት መልካም ሥራ ስታመሰግናቸውና በጸሎትም ስታስባቸው ትኖራለች፡፡

ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር ነውና እግዚአብሔር ሥራውን የሚሠራበት ጊዜ አለው ተብሎ በመጻሕፍት እንደተጻፈው፤ ቅዱስነትዎና እኔ ዕድሜ ከጤና እግዚአብሔር አምላካችን ሰጥቶን ይህን ቀን ለማየት ስላበቃን ለእግዚአብሔር ልዩ ምስጋና ዘወትር እያቀረብን ወንድማማችነታችንንና መንፈሳዊ አባትነታችንን አጽንተን ከመኖር በስተቀር ሌላ ምን እንከፍለዋለን፡፡

በተለይም ቅዱስነትዎና እኔ የደረስንበት ይህ ዘመን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን አንድነት ሰላምና ፍቅር፣ የቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላምና አንድነት መሆኑን ልጆቻችን የሀገራችን መሪዎች በአጽንዖት በአደባባይ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለም ለሚኖሩት ኢትዮጵያውያን ሲመሰክሩና ሲናገሩ ከማየትና ከመስማት በላይ ምንስ የሚያስደስት የተቀደሰ ነገር ይኖራል፡፡

ሕዝበ እግዚአብሔር የሆነው ሕዝባችን ካልተረዳዳና ካልተመካከረ፣ በአንድ ሐሳብ ካልተጓዘ ጽኑ ፈተና ያገኘዋልና ለቤተ ክርሰቲያናችንና ለሕዝባችን እውነተኛ ጥቅም በዝግታ እየተመካከርንና፤ ሥራውን የበለጠ እያሻሻልን በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እንመራዋለን የሚል ጽኑ እምነት አለን፡፡

ለቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አንድነትና ፍቅር መሠረት የሆኑና በወንድማማቾች መካከል ያለውን የሐሳብና የአስተዳደር ልዩነት ታላቅ ፍቅር በተሞላበት የልጅነት መንፈስ አማካሪዎቻችን ሆነው ባላሰለሰ ጥረት ለዚህ ዕድል በማብቃታቸውና በመብቃታችን ኢትዮጵያ ዛሬም ለታሪክ የሚሠሩና የሚኖሩ የጀግኖች እናት መሆኗን ቀጣዩ ትውልድ በታሪክነት የሚጠቅሰውና የሚጽፈው ተግባር ይሆናል፡፡

ይህን የምንለው የቀደሙ አባቶቻችን ለቤተ ክርስቲያናችን ክብርና ልዕልና የለፉበትንና የደከሙበትን ጉዳይ የሚያሰናክል ሁናቴ ከ2 ዐሥርተ ዓመታት በላይ በአንዲቷ ቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ በአስተዳደርና በሲኖዶሳዊው አመራራችን ውስጥ የቆየውን የልዩነት ታሪክ ‹‹ወንድሞች በአንድነት ሊኖሩ፣ በአንድነት ሊመሩና ሊሠሩ በመስማማት የካህናትን፣ የምእመናንንና የወጣቶችን ዕንባ የሚያብስ ውሳኔ መወሰናችን፤

በእኛ ዘመነ ክህነትና ፓትርያርክነት መታወጁ እኛን እግዚአብሔር አምላክ የበለጠ እድለኞች ያደረገን ሲሆን ለሰማዕያኑ ካህናት፣ ምእመናንና ወራዙት እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያውያን ይህ መልካም ብሥራት ሲነገር በሕይወታቸው ያሉት በክብር ጐልምሰው ሲታዩ፤ በሞት የተለዩት አፅማቸው በወርቅ ቀለም ተጽፎ አብቦና አፍርቶ ትተዋቸው ለሄዱት ትውልዶች የታሪክ ውርስ ሆኖ ሲታወስ ይኖራል፡፡

በዚህ በዛሬው ቀን የቸርነት ባለቤት የሆነው አምላካችን እግዚአብሔር በመካከላችን በመገኘት የአንድ አባት የእግዚአብሔርና የአንዲት እናት የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ልጆች ዳግመኛ በፍቅር ማሰሪያነት ታስረንና ተጣምረን እግዚአብሔርን ማመስገንና ቤተ ክርስቲያናችንን ማገልገል መጀመራችን በምድር ሠራዊትና በሰማይ መላእክት ጭምር ታላቅ ደስታ እንደሆነ እምነታችን የጸና ነው፤ እግዚአብሔርንም ዕጹብ ድንቅ ብለን ከማመስገን በላይ ምን እንላለን፡፡

አሁንም ደጋግመን የምንለው ለዚህ ዋና ዓላማ የእርስ በእርስ መመካከርን፣ መግባባትን፣ ፍቅርን፣ ይቅርታንና አንድነትን፣ የሚጠይቅ ስለሆነ በቤተ ክርስቲያናችን ለምንመራቸውና ለምናገለግላቸው ሕዝበ ክርስቲያን ጉዳትና ጥቅሙን እያመዛዘን የምንመክርበት፣ በሀገራችን ኢትዮጵያ ውስጥም ሆነ በውጭው ዓለም ላለችው ለቤተ ክርስቲያናችን የሰላምና የአንድነት አስተዳደር የምንናስቀጥልበት ቀን ላይ መሆናችን የቅዱስ ሲኖዶስ የወል የሰላምና የፍቅር ድል የተበሠረበት ዕለት ነው፡፡ የፍቅርና የሰላም የአንድነት ጠላት የሆነው ዲያቢሎስ በአደባባይ የተረታበት ዕለት መሆኑንም የምንናገረው በዚሁ ዕለት ነው፡፡

ከዚሁ ጋር የማይዘነጋው ጉዳይ ቢኖር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ ቅዱስነትዎና እኔ በተለይ በእግዚአብሔር ተመርጠንና ተጠርተን በ3ኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ እድ በአንድ ዕለት ተቀብተን በኤጴስ ቆጶስነት መሰየማችን ነባሩ የመነሻ ታሪካችን ነው፡፡ በተቀበልነውም የመስቀል መሸከም አደራ ቤተ ክርስቲያናችንን ስናገለግል ቆይተን ለዚሁ ለታላቁ ክብር ላበቃን አምላክ በአንደበታችን ብቻ ማመስገን አይበቃንም፡፡ ለዘለቄታ ቀዋሚ፣ ለትወልድ ተሻጋሪ፣ ለሰው ሁሉ በፍቅር የሚደርስ እኛ ጀምረን መጨረሱን ለእግዚአብሔር የምንሰጥበት ታላቅ የአደራ መቀበያና መስጫ፤ እንዲሁም ፍቅረ እግዚአብሔር ከፍቅረ ቢጽ ጋር ተዋሕዶ የተከበረበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡

ስለዚህ የቤተ ክርስቲያናችንን አስተዳደራዊ ሥራ በማሻሻል፡፡ በካህናት፣ በምእመናንና በወጣቶቻችን መካከል የሠለጠነ አሠራር በመትከል ስለ ሀገራችንና ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ ልማትና እድገት የምንደክም የሥራ ተከፋዮች እንሆናለን፡፡

ቅዱስ አባታችን!
በጤናና በሕይወት ጠብቆ ለዚህ ዕለት አድርሶ ወደ ቅድስት ሀገርዎ ኢትዮጵያ ለመግባት እንኳን አበቃዎ እያልኩ ንግግሬን “ኅሱ ሰላማ ለሀገር — ለሀገራችሁ ሰላምን እሹ” የሚለውን ለመፈጸም “ናሁ ሠናይ ወናሁ አዳም ሶበ ይሄልዉ አኀው ኅቡረ” ለሚለው ዘይቤ ተገዥዎች ሆነን ቤተ ክርስቲያናችንንና ተከታዮቻችንን እየመራን ሐዋርያዊ ተልእኮአችንን እንደምንፈጽም ያለንን እምነት እንገልጻለን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/a/wp-content/uploads/logo-am.svg tc32018-08-01 09:03:032025-01-27 09:05:36ሐምሌ 25 ቀን 2010 ዓ.ም. ለሃያ ሰባት ዓመታት በስደት ይኖሩ የነበሩት የኢትዮጵያ አራተኛ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በዕርቀ ሰላም እና በአንድነት ወደ ሀገራቸው ገብተዋል፡፡
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምርቃት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጡ
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ
  • መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
  • ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • April 2025
  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ሐምሌ 23 ቀን 2010 ዓ.ም በአባቶች መካከል በተፈጠረው ልዩነት የተላለፈው ቃለ ውግዘት ተነሣ Link to: ሐምሌ 23 ቀን 2010 ዓ.ም በአባቶች መካከል በተፈጠረው ልዩነት የተላለፈው ቃለ ውግዘት ተነሣ ሐምሌ 23 ቀን 2010 ዓ.ም በአባቶች መካከል በተፈጠረው... Link to: ሐምሌ 28 ቀን 2010 ዓ.ም. አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ በሲኖዶሳዊ ዕርቅ፣ በሰላምና በአንድነት ወደ ሀገራቸው መግባታቸውን አስመልክቶ መንግሥት በሚሊኒየም አዳራሽ ከፍተኛ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡ Link to: ሐምሌ 28 ቀን 2010 ዓ.ም. አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ በሲኖዶሳዊ ዕርቅ፣ በሰላምና በአንድነት ወደ ሀገራቸው መግባታቸውን አስመልክቶ መንግሥት በሚሊኒየም አዳራሽ ከፍተኛ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡ ሐምሌ 28 ቀን 2010 ዓ.ም. አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top