• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

34ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከጥቅምት 8-11 ቀን 2008 ዓ.ም አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡

October 22, 2015

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያው ኀላፊዎችና፣ የየድርጅቱ ሥራ አስኪያጆች፤ የየአህጉረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጆች፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የካህናት፣ የምእመናንና የሰንበት ት/ቤት ተወካዮች፣ ክቡራን የዚህ ታላቅ ጉባኤ ተሳታፊዎች፤

ሁሉን ፈጥሮ የሚገዛ አምላካችን እግዚአብሔር ያለፈውን የ2007 ዓ.ም.የሥራ ዘመን በሰላም አስፈጽሞ በአዲሱ የ2008 ዓ.ም. ልንሠራው የሚገባንን ሥራ ለመሥራት አንድ ላይ ስለሰበሰበን ከሁሉ በፊት እርሱን እያመሰገን እንኳን ለሠላሳ አራተኛው ዓመታዊ መደበኛ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በሰላም አደረሳችሁ እንላለን ፡፡

‹‹ቃለ እግዚብሔር ቃል ንጹሕ — የእግዚአብሔር ቃል ንጹሕ ቃል ነው።›› (መዝ. 11፥6)

ስለ ቃል አንሥተን ስንመረምር በፍጡራን ዘንድ የተለያዩ ቃላት እንዳሉ ከቅዱስ መጽሐፍ እንመለከታለን፡፡ ከእነሱ መካከል የተወሱትን ለመጥቀስ የአዕዋፍን ቃል “ቃለ ማዕነቅ” የውኃን ቃል “ቃለ ማያት ብዙኅ” የደመናትን ቃል “ቃለ ወሀቡ ደመናት” እየተባለ በቅዱስ መጽሐፍ ተጽፎአል፡፡

ከምድራውያን ፍጡራን ሁሉ የተሻለ ቃለ ሰብእም እንዳለ ሁላችን የምናውቀው ጉዳይ ነው፡፡ ነገር ግን ከዚህ ሁሉ የበለጠና ሕያው የሆነው ቃል የእግዚአብሔር ቃል ነው፤ ቃለ እግዚአብሔር በሰማይም ሆነ በምድር ያሉትን ማለትም የሚታዩትንና የማይታዩትን ሁሉ የፈጠረ፤ ኀይላተ ሰማያት ወምድር ጸንተው የሚኖሩበት፣ ሁሉን የሚያሳልፍ እንጂ እርሱ የማያልፍ ቃል ነው፤ የእግዚአብሔር ቃል እውነት እንጂ ሐሰት የማይቀላቀልበት፤ ኀይል እንጂ ድካም የማይፈራረቅበት በመሆኑ ንጹሕ ቃል ይባላል፡፡

በዚህ ዓለምም ሆነ በወዲያኛው ዓለም የእግዚአብሔር ቃል ያልተናገረለት ፍጡር የለም፤ ይሁን እንጂ የእግዚአብሔር ቃል ከሁሉም በላይ አብዝቶ የተናገረላት ብትኖር ቤተ ክርስቲያን ብቻ ናት፣ በተለያየ ሕብረ ትንቢት ወአምሳል፣ በተለያየ ኊልቈ ሱባዔ ወቀመር ተጽፎ የሚገኘው ቃለ እግዚአብሔር የመጨረሻ መዳረሻው ቤተ ክርስቲያን ናት፤ ቤተ ክርስቲያን በጥንተ ፍጥረት ከመጀመሪያ ጀምሮ ነበረች፤ ከዓለም ፍጻሜ በኋላም የእግዚአብሔር መንግሥት ርእሰ ከተማ ሆና ማኅለቅት በሌለው ኊልቈ ዘመን ትቀጥላለች፡፡

የእግዚአብሔር ቃል በብሉይ ኪዳን ስለ ቤተ ክርስቲያን ሲናገር “ይሰግዱ ለኪ ኵሎሙ ነገሥታተ ምድር ወይልሕሱ ጸበለ እግርኪ፤ ወትሰመይ ጽዮንሃ ሀገረ እግዚአብሔር፤ ወአስተጋብኦሙ ለውሉድኪ በውስቴትኪ፣ ያመጽኡ አምኃኪ እምርሑቅ ብሔር ወነገሥት ክብረ ሊባኖስ” ብሎአል፡፡ ይህም ማለት ሁሉም የምድር ነገሥታት ላንቺ ይሰግዳሉ፤ የእግርሽንም ትቢያ ይልሳሉ፤ አንቺ የእግዚአብሔር ከተማ ጽዮን ነሽ ትባያለሽ፤ ልጆችሽን በአንቺ ውስጥ እሰበስባቸዋለሁ፤ መባውን፣ ቀዳምያቱን፣ ዐሥራቱን፣ በኵራቱን ከሩቅ አገር ይዘውልሽ ይመጣሉ፤ ነገሥታትም የሊባኖስን ክብር ያመጡልሻል ማለት ነው ፡፡ (ኢሳ. 49፡23)

በውስጧ ሆነው ሲያገለግሉ የሚኖሩ ልጆችዋም ‹‹ወይትወሀውሁ በአዝማን ዘአልቦ ኊልቁ፤ ፍጻሜ በሌላቸው አዝማነ መንግሥተ ሰማያት ሲመላለሱ ይኖራሉ›› ተብሎ (በመጽ ምሥ.) በተነገረላቸው ቃል መሠረት ማኅለቅትና ፍጻሜ በሌለው ሕይወት በውስጧ ለዘለዓለሙ በደስታና በክብር ይኖራሉ፤ እንግዲህ የእግዚአብሔር ቃል ይህን ሁሉ የተናገረው ለንጽሕትና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ነው፤ ዛሬ በዚህ ዐቢይ ጉባኤ እግዚአብሔር የሰበሰበን ኀይል ‹‹ልጆችሽን በአንቺ ውስጥ እሰበስባቸዋለሁ›› ብሎ ከዛሬ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ዓመታት በፊት የተናገረው የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ዛሬ መባዉን፣ ቀዳምያቱን፣ በኵራቱን፣ ዐሥራቱን፤ ወይም በዘመናችን አነጋገር የሰበካ ጉባኤ አስተዋፅኦውን ከሩቅ አገር ይዘን ወደዚህ የመጣንበት ምክንያት ‹‹መባሽን ከሩቅ ይዘውልሽ ይመጣሉ›› የሚለው የእግዚአብሔር ቃል አስተምሮን ነው፤ ይህ ሕያውና የማይታበል ቃል ዛሬም በእኛ ውስጥ ሥራውን እየሠራ የሚገኝ በመሆኑና እኛም የቃሉ መሣሪያ ሆነን በመገኘታችን እጅግ፤ ደስ ሊለን ይገባል፡፡

በዓለም ውስጥ እጅግ ሀብታምና ኀያል የሆነ ማን ነው? ተብሎ ቢጠየቅ ትክክለኛ መልስ ሊሆን የሚችለው ቤተ ክርስቲያን ናት የሚለው መልስ ነው፡፡ እርግጥ ነው፤ ቤተ ክርስቲያን ለሰዎች ኀይል ቀርቶ ለሰይጣንና ለሠራዊቱ እንኳ የማትበገር ኀያል ናት፤ በዚህም የእግዚአብሔር ቃል ‹‹ወአናቅጸ ሲኦል ኢይኄይልዋ፣ የሲኦል በረኞች ሰይጣንና ሠራዊቱ አያሸንፉአትም›› ብሎ ተናግሮላታል፤ ይህ ቃል የማይሸነፍ ኀያልና ንጹሕ የእግዚአብሔር ቃል ስለሆነ እነሆ ጠላቶቿ ሁሉ እየተሸነፉ እርስዋ ግን በድል አድራጊነት በዘመኑ ሁሉ ወደፊት እየገሠገሠች ከዘመናችን ደርሳለች፤ ወደፊትም በዚሁ ትቀጥላለች፡፡

በሌላም በኩል ቤተ ክርስቲያን እጅግ የበለጸገች ባለሀብት መሆንዋን የእግዚአብሔር ቃል ሲናገር “ወይበውእ ኀቤኪ ብዕለ አሕዛብ፤ የሕዝቡና የአሕዛቡ ብዕል ወዳንቺ ይገባል” ይላል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ይህ ቃል መሠረተ ሀብቷ ሆኖ አስገዳጅ ምድራዊ ኀይል ሳይኖር በቃሉ ቀስቃሽነት ብቻ ሕዝበ እግዚአብሔር የሆኑ ክርስቲያኖች ያላቸውን በደስታ፣ በፈቃደኝነትና በልግስና ዐውደ ምሕረቷ ድረስ እየመጡ ከከበረው የወርቅ ጌጥ ጀምሮ ስጦታውን በየዐይነቱ ሲያፈሱላት ይኖራሉ፡፡ እንግዲህ ይህን ሁሉ በዐይናችን እየተመለከትን የምንገኝ እኛ ‹‹በአማን ኢይሔሱ ቃሎ ዘነበበ፣ በእውነት የተናገረውን ቃል አይዋሽም›› ብለን እርሱን ከማመስገን ጋር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆነን ልንፈጽመው የተሰጠንን ተልእኮ በደስታ፣ በፈቃደኝነት፣ በትጋትና በቅንነት ከመወጣት በቀር ሌላ ምን ሥራ ሊኖረን ይችላል፤ ከዚህ ተነሥተን ስናይ እግዚአብሔር ለቤተ ክርስቲያን የተናገረው ቃሉን እንዳላጠፈብን እናረጋግጣለን፡፡
በአንጻሩ ደግሞ እኛስ ቃላችንን አክብረናል፤ ወይስ አጥፈናል፤ የሚለውን መመርመር ከእኛ ይጠበቃል፡፡

በአሁኑ ጊዜ ያለው የቤተ ክርስቲያናችን ገቢ በቂ ነው ባይባልም ቤተ ክርስቲያናችን በሰበካ ጉባኤ መደራጀት ስትጀምር ገቢዋ በመቶ ሺሕ ብር ደረጃ የነበረው ዛሬ ወደመቶ ሚሊዮኖች መድረሱ በሀገር ዐቀፍ ደረጃ አጠቃላይ ሲታይ ደግሞ ወደ ቢሊዮኖች መድረሱ ትልቅ እድገት ነው፤ ነገር ግን የምእመናን እድገትስ የት ነው ያለው የሚለውን አይተነዋል ወይ?፤ በዚህ በኩል ያለው እድገት የኋልዮሽ መሆኑ የማያውቅስ በመካከላችን ይኖር ይሆን? ይህን ችግር በሚገባ ተገንዝበንና በቁጭት ተነሣሥተን ነገሩን ለመቀልበስ ያደረግነው ሙከራስ ይኖር ይሆን? ለዚህ ጥያቄአችን ከዚህ ጉባኤ መልስ እንፈልጋለን ፡፡

መቼም ቢሆን ተልእኮአችን ሰማያዊ እንጂ ምድራዊ እንዳይደለ ሁላችንም እናውቃለን፤ ሰማያዊውና ታላቁን ተልእኮአችን በተገቢው ሁኔታ ለመወጣት ከኅሊና መቈርቈር ጀምሮ እስከ ኅልፈተ ሕይወት የሚዘልቅ የመሥዋዕትነት ዋጋ እንደሚጠይቅ ምንጊዜም አንዘነጋውም፤ ይህ መሥዋዕትነት ብዙዎቹ የሃይማኖት መስተጋድላን አባቶቻችን ያለፉበት ስለሆነ ለኛ ለቤተ ክርስቲያን ልጆች አዲስ አይሆንም፡፡ ይሁንና እኛ ባለንበት በአሁኑ ዘመን ከፍተኛ መሥዋዕትነትን እየጠየቀን ያለው የደምና የሕይወት መሥዋዕትነት ሳይሆን ራስን የመካድ ወይም ያልተገባ ጥቅምን የመጸየፍና ኀላፊነትን በሚገባ ለመወጣት የመነሣሣት ጉዳይ ነው፡፡

ቤተ ክርስቲያናችንን ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ጋር ስናነጻጽር በቊጥር እጅግ የላቀ የውሉደ ክህነት ብዝኅነት ያላት ስትሆን ‹‹ታላቁን የቅዱስ ወንጌል ተልእኮን›› ለውሉደ ሰብእ በማዳረስ ረገድ ያለን ውጤት ግን አናሳ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ባሕርን አቋርጦ፣ ድንበርን ተሻግሮ፣ እስከ ጽንፈ ምድር ተጒዞ፣ አስተምሮና ያላመነውን፣ አሳምኖ የቤተ ክርስቲያን ልጅ ማድረጉ ይቅርና በሀገር ውስጥ ያሉትን ወገኖች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አሰባስቦ ምእመናንን ማብዛት ብዙ ያልተሄደበት እንደሆነ ማወቅ አለብን፡፡

ከሁሉም በላይ የሚያስቈጨው ደግሞ ትናንት ቤተ ክርስቲያን “ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና” ሰጥታ በአባልነት የተቀበለቻቸው ልጆችዋ ዛሬ እናት ቤተ ክርስቲያናቸውን እየካዱ ወደሌላው ጎራ የመቀላቀሉ ጉዳይ እጅግ በጣም እየናረ መምጣቱን ነው፡፡

የምእመናን ፍልሰት በየጊዜው እየጨመረ የመሄዱ መነሻ ምሥጢር ምንድን ነው? የሚለውን ጥያቄ ቤተ ክርስቲያናችን በአጽንዖት ልታጤነው ይገባል፤ በዚህ ዙሪያ የሚታየው ክፍተት ፈጣን ምላሽ በመስጠት መግቻ ካላበጀንለት ነገ ከባድ የሃይማኖትና የታሪክ ወቀሳ ማስከተሉ እንደማይቀር ልብ እንበል፡፡ ለመሆኑ ምእመናን ከቤተ ክርስቲያናችን እየወጡ ወደ ሌላ ካምብ ለመግባት ለምን መረጡ?
• የሚያስተምራቸው ካህን አጥተው ነው?
• የቤተ ክርስቲያናችን ትምህርተ ሃይማኖት ክፍተት ኖሮት ነው?
• የቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደር የማያረካ ሆኖ ነው?
• የካህን እጥረት ስላለ ነው?
• ወይስ ሌሎች ከእኛ የተሻሉ ሆነው ስለተገኙ ነው?

የዚህ ሁሉ መልስ በእያንዳንዳችን ኅሊና ውስጥ ቊልጭ ብሎ ስለሚታወቅ የጥያቄው መልስ ለእናንተው ሰጥተናል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ዐቢይ ጉባኤ በሁለት ዐበይት የቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ትኲረት ሰጥቶ እንዲነጋገርባቸው ሳንጠቁም አናልፍም ይኸውም፡-
• ምእመናንን የመጠበቅ ተልእኮ በሚገባ እየተወጣን አይደለምና ባዶአችንን ከመቅረታችን በፊት ለተደራጀና ለድንበር የለሽ ትምህርተ ወንጌል ብንነሣ፤
• የአስተዳደር ሥራችን ለምእመናን ኅሊና ዕንቅፋት እየሆነ ነውና የሃይማኖቱን መርሕ ጠብቀን አስተዳደራችን የሕግ የበላይነትን ያረጋገጠ፣ ግልጽ፣ ተአማኒና ተጠያቂነትን ያሰፈነ የምእመናንን ልብ የሚያረካ፣ ምእመናን በቤተ ክርስቲያናቸው ኵራት እንዲሰማቸው የሚያስችል አሠራር ብናረጋግጥ ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ እንችላለን፤
• ይህ ሲሆን ነው የሰበካ ጉባኤ ዐላማ ግቡን የሚመታው በእርግጠኝነት ለመናገር እንደ ጌታችን አስተምህሮ ሕፃናትን፣ ወጣቶችንና ዐዋቂዎችን በአግባቡ ጠብቃ የምትኖር ቤተ ክርስቲያን ለሃይማኖት ቅሰጣ አትጋለጥም ፡፡

ስለሆነም የሰበካ ጉባኤ ዋና ምንጭ ምእመናን መሆናቸውን ዐውቀን በዚህ ዙሪያ በሰፊው እንሥራ፤ ቢቻል አሁን አለን ከምንለው የላቀ የምእመናን ቊጥር በበለጠ ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት ማድረግ፣ ባይሆን ደግሞ ባለበት ጠብቆ ለማቆየት በርትተን መሥራት ይጠበቅብናል ፡፡

በመጨረሻም፡ ይህ ዓለም አቀፋዊ የቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ከየአቅጣጫው የሚቀርቡትን ሪፖርቶች በመገምገም፣ ለበጀት ዓመቱ ሥራችን መሠረት የሚሆኑ የዕቅድ አመላካች አስተያየቶችና ሐሳቦችን በማስቀመጥ፣ እንደዚሁም የሀገራችንን የሕዳሴ ጒዞ በተያዘለት መርሐ ግብር መሠረት ግቡን እንዲመታ ሕዝቡን ለማነሣሣት ቃል በመግባት የሚጠበቅበትን ሁሉ እንዲያደርግ መልእክታችንን በቤተ ክርስቲያን ስም እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ፣ ይቀድስ አሜን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32015-10-22 14:43:132025-01-28 14:44:2234ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከጥቅምት 8-11 ቀን 2008 ዓ.ም አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: መስከረም 16 ቀን 2008 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓል (የእስክንድርያ ፓትርያርክ መገኘት ጋር) Link to: መስከረም 16 ቀን 2008 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓል (የእስክንድርያ ፓትርያርክ መገኘት ጋር) መስከረም 16 ቀን 2008 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓል (የእስክንድርያ... Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top