• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

October 23, 2015

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት
የአማልክት አምላክ፣ የነገሥታት ንጉሥ፣ የአጋእዝት ጌታ የሆነው እግዚአብሔር አምላካችን ከተለያዩ የዓለም አህጉርና ከሀገራችን አህጉረ ስብከት አሰባስቦና አንድ ላይ አገናኝቶ በመንፈስ ቅዱስ ስለተሰጠን ሐዋርያዊ ተልእኮ ለመወያየት ስለሰበሰበን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን፡፡

“ምንተ ይቤ መንፈስ ቅዱስ ለአብያተ ክርስቲያናት፤ መንፈስ ቅዱስ አብያተ ክርስቲያናትን አስመልክቶ ምን አለ?” (ራእ. 2፥7)፡፡

በጌታችን በአምላካችንና በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተችው ክርስቶሳዊት ቤተ ክርስቲያን ከበዓለ ኃምሳ ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ አመራርና ጥበቃ ሥር እንዳለች ይታወቃል፡፡ ቅዱስ መንፈሰ እግዚአብሔር ዓለም በማያየውና በማያውቀው ረቂቅ ጥበቡ በሃይማኖት አማካይነት በልበ ምእመናን አድሮ ቤተ ክርስቲያንን ሲመራ ይኖራል፡፡ ከዚህም ሌላ በሥዩማነ ቤተ ክርስቲያን አማካይነት ቅዱስ ቃሉንና ቅዱሳት ምሥጢራቱን ለምእመናን ያድላል፡፡ በመሆኑም ሥዩማነ ቤተ ክርስቲያን፤ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን መሪ የሆነው መንፈስ ቅዱስ የሚለውንና የሚናገረውን በትክክል አዳምጠውና ተረድተው ምግብናቸውን ማከናወን እንዳለባቸው ለሰባቱ ሥዩማነ ቤተ ክርስቲያን ዘእስያ የተነገረው ቃለ ተግሣጽ ወምዕዳን በግልጽ ያስተምረናል፡፡

ለተጠቀሱት የቤተ ክርስቲያን ሥዩማን የተላለፈው መልእክት በአጠቃላይ የመንፈስ ቅዱስ ቃል እንደሆነ ለማመልከት ‹‹ምንተ ይቤ መንፈስ ቅዱስ ለአብያተ ክርስቲያናት›› በሚልና ‹‹ዘቦ እዝን ሰሚዐ ለይስማዕ›› በሚል ኀይለ ቃል ሲዘጋ እናያለን፡፡

ለሰብዑ አብያተ ክርስቲያናት ዘእስያና ለአለቆቻቸው የተነገረው ሁሉ ዛሬ ያለችው ቤተ ክርስቲያንና አለቆቿን ጭምር በቀጥታ የሚመለከት እንደሆነ ጥርጥር የለውም፡፡ ከአለቆቹ መካከል የተመሰገኑም፣ በመካከለኛ ደረጃ የሚገኙም፣ እንደዚሁም ጠንከር ያለ ተግሣጽ የደረሰባቸው እንዳሉ እንገነዘባለን፡፡ ዛሬ በቤተ ክርስቲያን የሥራ ኀላፊነት የምንገኝ ሥዩማንም በዚያን ጊዜ በነበረችው ፈታኝ ዓለም ውስጥ የምንገኝ እንደመሆናችን መጠን፤ በዚያን ጊዜ የነበሩ ኩነቶች ሁሉ አሁንም አይኖሩም ማለት አይቻልም፡፡

በየትኛውም ዘመን፣ በየትኛውም ቦታ፣ ክፍተት አይፈጠርም ብሎ ሙሉ በሙሉ ኀላፊነት መውሰድ የሚችል ይገኛል ተብሎም አይጠበቅም፡፡ ነገር ግን የከፋና የባሰ ክፍተት እንዳይፈጠር የተጠናከረ ሥራ በመሥራት መከላከል የሚችሉ በየጊዜው ሁሉ የተነሡ ታላላቅ አበው እንዳሉ እናስተውላለን፡፡ በዚህ ዘመን የምንገኝ ኖሎትም ምንም ቢሆን ከዚህ እውነታ ውጭ መሆን አንችልም፤ መሠረታዊ ችግር ሊሆን የሚችለው ክፍተት ለምን ተፈጠረ የሚለው ሳይሆን ክፍተት መኖሩ እየታወቀ ዝም ብሎ መኖሩ ነው፡፡ በዚህ ዙሪያ ይህ ዐቢይ ጉባኤ ብዙ መሥራት ይጠበቅበታል፡፡

እንደ እውነቱ ከሆነ በቤተ ክርስቲያናችን መሠራት የነበረባቸው፤ ሆኖም ግን እስካሁን በአጥጋቢ ሁኔታ ያልተሠራባቸው የሥራ መስኮች እንዳሉ ባይካድም ጥሩ ውጤት ያስመዘገብንባቸው ነገሮች እንዳሉም መዘንጋት የለበትም፤ በተለይም ሕዝበ ክርስቲያኑ ባለው ዐቅም ሁሉ ቤተ ክርስቲያኑን ለመደገፍና ለማልማት የሚያደርገው ቀና ትብብር ከመቼውም ጊዜ የበለጠ ተስፋ ሰጪ ሆኖ ይታያል፣ አንዳንድ አህጉረ ስብከትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በሚያስደንቅ ሁኔታ የራስ አገዝ ልማት እያካሄዱ ለቤተ ክርስቲያናችን ተጨማሪ የሚሆን ትልቅ ዐቅም እየፈጠሩ ይገኛሉ፡፡

ከሁሉም በላይ ደግሞ የቤተ ክርስቲያናችንን ሐዋርያዊ ተልእኮ ለማስፋፋት በዓለም ዙሪያ የተደረገው እንቅስቃሴ በአሁኑ ጊዜ ሁሉንም ክፍለ ዓለማት ማለትም ከምዕራብ አሜሪካ እስከ ጃፓን፣ ከአየርላንድ እስከ አውስትራሊያ ቤተ ክርስቲያናችን ክንፎቿዋን የዘረጋችበት ሁኔታ የተፈጠረ በመሆኑ ትልቅ ስኬት ተገኝቶአል ማለት እንችላለን፤ ቤተ ክርስቲያናችንም ዓለም አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን ወደ መሆን አድጋለች ማለት ይቻላል፡፡

የቤተ ክርስቲያናችን ሥራ ሰፊና ዘርፈ ብዙ በመሆኑ አሁንም ቢሆን ትኵረት ተሰጥቶአቸው በቅድሚያ ሊሠሩ የሚገቡ ሥራዎች እንዳሉ ማስታወሱ ተገቢ ነው፤ በመሆኑም፤

• ቤተ ክርስቲያናችን ዘመኑን የዋጀ የአስተዳደር ጥበብ ተከትላ ሀብትዋና ንብረትዋን መጠበቅ የሚያስችሏትን አሠራሮች መቀየስ፤
• በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ መሠረት ሊዘጋጁ የሚገቡ ልዩ ልዩ ደንቦች፣ ፖሊሲዎችና መመሪያዎችን በማዘጋጀት ሥራዎች ሁሉ ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲኖራቸው ማድረግ፤
• ቀደም ሲል ተጀምሮ የነበረውንና እስካሁን በይደር የቆየውን የመሪ ዕቅድና የሚድያ ጥናት በዚህ ዓመት በጀት ተይዞለት በአፋጣኝ ሥራ ላይ ማዋል፤
• የምእመናንን ፍልሰት ለማስቆም መልካም አስተዳደርን በማስፈን ስብከተ ወንጌልን ማጠናከር፣
• በውጪ ሀገራት የሚገኙ አድባራት ከእናት ቤተ ክርስቲያን ጋር ያላቸውን ግንኙነትና ትስስር ማጠናከር፤
• በሁሉም አቅጣጫ የልማት ሥራዎችን በማስፋፋት ቤተ ክርስቲያናችንን በኢኮኖሚ የበለጸገች ማድረግ፤
• የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ የሆኑ ሕፃናትና ወጣቶች በሰንበት ት/ቤት በስፋት እየተደራጁ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር ተገንብተው እንዲያድጉ ማድረግ፤
• ለአብነት ት/ቤቶችና ለገዳማት የሚደረገውን ድጋፍ በማሳደግ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ማድረግና በመሳሰሉት ሥራዎች ልዩ ትኲረት ሰጥተን የምንሠራባቸው ሥራዎች ሊሆኑ ይገባል፡፡
• በሌላ በኩል በዚህ ዓመት በሀገራችን በተከሠተው የዝናም እጥረት ምክንያት፣ በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ድርቅ እንደተከሠተና የምግብ እጥረትም እንዳጋጠመ፣ በሠላሳ አራተኛው የቤተ ክርስቲያናችን አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በቀረቡ የየአህጉረ ስብከቱ ሪፖርቶች ለመገንዘብ ተችሎአል፡፡
• በመሆኑም ለወገን ደራሽ ወገን ነውና በተለመደው ሃይማኖታዊና ማኅበራዊ ባህላችን መሠረት፣ ሕዝቡ ካለው እየከፈለ የተጎዱ ወገኖችን እንዲረዳ ከማስተማርና ከማስተባበር በተጨማሪ፣ የሕዝብ እናት የሆነችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖቻችን ዐቅሟ የሚችለውን ሁሉ ታደርግ ዘንድ፣ ይህ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በጉዳዩ መነጋገር አለበት፡፡

በመጨረሻም፡ ይህ ሐዋርያዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ዐቢይ ጉባኤ ሐዋርያዊት፣ ህልውተ ኵሉ፣ አንዲትና ቅድስት የሆነችው ቤተ ክርስቲያናችን በሁሉም አቅጣጫ የተሟላ፤ የተስተካከለና ከክርስቶሳዊ አስተምህሮዋ ጋር የሚጣጣም አሠራር እንዲኖራት ከላይ የተጠቀሱትን ዋና ዋና ጉዳዮች አንሥቶ በመወያየት ጠቃሚ ውሳኔዎችን ያሳልፍ ዘንድ በማሳሰብ በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 164 በተደነገገው ቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የ2008 ዓ.ም. የጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤን ባርከን ከፍተናል፡፡

እግዚአብሔር ጉባኤችንን ይባርክ፤ይቀድስ አሜን

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32015-10-23 08:22:082024-12-07 08:27:32ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: 34ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከጥቅምት 8-11 ቀን 2008 ዓ.ም አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ Link to: 34ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከጥቅምት 8-11 ቀን 2008 ዓ.ም አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ 34ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከጥቅምት... Link to: ጥቅምት 12 ቀን እስከ 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ Link to: ጥቅምት 12 ቀን እስከ 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ ጥቅምት 12 ቀን እስከ 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተካሄደው...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top