• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ጥቅምት 12 ቀን እስከ 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡

November 2, 2015

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በመደበኛ ስብሰባ፤ በዓመት ሁለት ጊዜያት እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ተራ ቍጥር 164 በተደነገገው መሠረት የመክፈቻው ሥርዐተ ጸሎት ከተፈጸመበት ከበዓሉ ዋዜማ ከጥቅምት 11 ቀን ጀምሮ እስከ ጥቅምት 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረስ ለዐሥራ ሁለት ቀናት ያህል ባደረገው ስብሰባ፡ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን እንዳይፋለስ ለመጠበቅና ለመቈጣጠር፤ ካህናት በመንፈሳዊው ተልእኮአቸው እንዲፋጠኑ ለማስተባበር፤ ምእመናን በምግባር፣ በሃይማኖት ጸንተው እንዲኖሩ ለማስተማር፤ እግዚአብሔር የሚመሰገንበትን፣ ቤተ ክርስቲያን የምትገለገልበትን ሥርዐት ለመወሰን፤ ቅዱስ ሲኖዶስ ሥራውን በጸሎት ጀምሮአል፡፡

1. ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. በተጀመረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የተደረገውን የመክፈቻ ንግግር በቤተ ክርስቲያኒቱ እየተሠሩ ያሉትን የሥራ ሂደቶች የዳሰሰና በሁሉም አቅጣጫ ቤተ ክርስቲያኗ የደረሰችበትን እድገትና ሊሠራ የሚገባውን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት በሚገባ የሚያስገነዝብ በመሆኑ፤ እንዲሁም በሀገራችን በአንድ አንድ አካባቢ በተፈጠረው የዝናም እጥረት ምክንያት በተከሠተው ድርቅ ለተጐዱ ወገኖች ሊደረግ ስለሚገባው ሰብኣዊ አገልግሎት ርዳታንና ትምህርትን ለመስጠት የሚያስችል አባታዊ መመሪያ በመሆኑ ተግባራዊ እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
2. በተለያየ ጊዜና ምክንያት ኢትዮጵያ ሀገራችንን ድርቅ እያጠቃት ጥቂት የማይባሉ የሀገሪቱ ዜጎች ለረሀብ ሲጋለጡ፣ እኛ ኢትዮጵያውያን በተለመደው የመተሳሰብና የመረዳዳት ባህላችንን በተግባር በማሳየት፣ ፈታኝ ችግሮችን ማሳለፋችን ይታወቃል፡፡ በአሁኑም ጊዜ በዝናም ዕጦት ምክንያት በሀገራችን በአንዳንድ አካባቢ በተከሠተው ድርቅ ምክንያት ለረኃብ የተጋለጡ ወገኖቻችንን ለመታደግ መንግሥት እያደረገ ያለውን ከፍተኛ ጥረት ቅዱስ ሲኖዶስ በማድነቅ ቤተ ክርስቲያናችንም የተለመደውን አስፈላጊ እገዛና ድጋፍ ማድረግ ስላለባት፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ፣ በአንድ ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ የሚመራ ዐቢይ ኮሚቴ ተቋቁሞ ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትና ድጋፍ ሰጭ በጎ አድራጊዎች ጋር በመቀናጀት የርዳታ ሥራውን እንዲያፋጥን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
3. የመልካም አስተዳደር ዕጦትንና የሙስና መስፋፋትን አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ በጉዳዩ ሰፊ ውይይት በማድረግ፣ እንዲህ ዐይነቱ ሀገርንና በአጠቃላይም የሰውን ልጅ ሁሉ የሚያጎድፍ ክፉ ተግባር በመሆኑ ሀገርንና ወገንን እንዳይጐዳ አጥብቆ መከላከል አስፈላጊ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያኒቱ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ በዚህ ጉዳይ ላይ አጥብቃ እንድታስተምር፣ ይህ የመልካም አስተዳደር ዕጦትና የሙስና መስፋፋት የችግሩ መነሻና መፍትሄ መታወቅ ስላለበት አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያኗን ሁለንተናዊ ችግር የሚያጠና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ያካተተ 9 አባላት ያሉበት ዐቢበይ ኮሚቴ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ተቋቁሟል፡፡
4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአገር ባለውለታ እንደመሆኗ ለዘመናት ሕዝቡን ስለ ሰላም፣ ስለ ልማት፣ ስለ አገር ፍቅርና ስለአብሮነት ጊዜው በፈቀደው መንገድ ሁሉ ስታስተምር ቆይታለች፡፡ አሁንም ዘመኑ ባፈራው መገናኛ ብዙኃን አብዛኛውን ኅብረተሰብ በትምህርት ለመድረስ እንዲያስችላት የመገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ስርጭት መጠቀም እንድትችል በባለሙያዎች ተዘጋጅቶ የቀረበውን ጥናት እና ብር12,000,000 (ዐሥራ ሁለት ሚሊዮን ብር) የአንድ ዓመት በጀት ቅዱስ ሲኖዶስ አጽድቋል፡፡
5. የዕድሜ ባለጸጋ የሆኑ አረጋውያን የሚጦሩበትን፤ በተለያየ ምክንያት ወላጆቻቸውን ያጡ ዕጓለ ማውታ ሕፃናት የሚያድጉበትን የምግባረ ሠናይ ተቋማትን ያላቋቋሙ አህጉረ ስብከት እንዲያቋቁሙ፤ አቋቁመው አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት አህጉረ ስብከትም አጠናክረው እንዲቀጥሉ መመሪያ ተሰጥቷል፤
6. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመማር ማስተማር ሥርዐትን በመዘርጋት በአገር ደረጃ የትምህርት መሠረት መሆኗ ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ጊዜም በቤተ ክርስቲያኒቱ የተከፈቱና የመማር ማስተማር ሥራውን እያከናወኑ ያሉ ሦስቱ መንፈሳዊ ኮሌጆች ተማሪዎችን አስተምሮ ለቁም ነገር በማብቃት ቤተ ክርስቲያንና አገርን እንዲጠቅሙ፣ ለኅብረተሰቡ የምሥራች ተናጋሪና ሰላምን የሚሰብኩ ሁነው እንዲያድጉ ለማድረግና ኮሌጆቹን ለበለጠ እድገት ማብቃት በሚያስችልበት ሁኔታ የኮሌጁን የውስጥ ይዘት እንዲያጠኑ 3 ብፁዓን አባቶችን ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡
7. ቤተ ክርስቲያኒቱ በማታውቀው ሁኔታ የቤተ ክርስቲያኒቱን ፈቃድ ሳያገኙ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም ትምህርታዊ ስብከት የሚያስተላልፉ ዝማሬ የሚያሰሙ መጻሕፍት፣ መጽሔቶችና ጋዜጦች ልዩ ልዩ በራሪ ወረቀቶችን የሚያሳትሙ ሁሉ በአገሪቱ ሕግ መሠረት በሕግ እንዲጠየቁ፣ ለሚመለከታቸውም የሚዲያ አካላት ማሳሰቢያ እንዲደርስ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
8. አንዳንድ የእምነት ተቋማት ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊትና ኦርቶዶክሳዊት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገልገያ የሆኑትን ንዋየ ቅድሳት፣ አልባሳት፣ መስቀሎች፣ መቋሚያ፣ ከበሮ፣ ጸናጽልና የመሳሰሉትን ሁሉ የራሳቸው ያልሆነውን የራሳቸው በማስመሰል እየተጠቀሙ መሆኑን ጉባኤው ተገንዝቦ በጉዳዩ ሰፊ ጥናት ቀርቦ ውሳኔ እንዲያገኝ ለማድረግ ለጥናቱ ብፁዓን አባቶችን ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡
9. በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም በየአህጉረ ስብከቱ ተቋቁሞ ለበርካታ ዓመታት ለአገርና ለወገን አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የሕፃናትና ቤተሰብ ጉዳይ ድርጅት በተለይ በአሁኑ ጊዜ በአገራችን በአንዳንድ ቦታ የተከሠተውን ድርቅ ታሳቢ በማድረግ አሳዳጊ ላጡና በድርቁ ምክንያት ችግር ለደረሰባቸው ሕፃጻናት የተለመደውን ሰብኣዊ አገልግሎት አጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
10. በየመንፈሳዊ ኮሌጆች መስፋፋትና ዕድገት ላይ የተነጋገረው ቅዱስ ሲኖዶስ ፡- በኦሮምያ፣ በጅማ ሀገረ ስብከትና በአማራ ክልል በባሕርዳር ከተማ ቤተ ክርስቲያኒቱ አዲስ የከፈተታቸው መንፈሳዊ ኮሌጆች ቤተ ክርስቲያናችን ከጥንት ጀምሮ የዘወትር ሥራዋ አድርጋ የያዘችውን የትምህርት ሥራ ማጠናከር እንዲያስችላት በመሆኑ የመምህራን ማሠልጠኛዎቹ የመማር ማስተማር ሥራቸውን ለኅብረተሰቡ በሚጠቅም መልኩ እንዲያስቀጥሉ ቅዱስ ሲኖዶስ አሳስቧል፡፡
11. ቤተ ክርስቲያናችን ቀጣይ ሥራዎቿን ሁሉ ካለፈው በበለጠ በመሪ ዕቅድ የተደገፈ በማድረግ ማከናወን እንዲያስችላት ለ2008 በጀት ዓመት የተዘጋጀውን መሪ ዕቅድና የዕቅዱ ማስፈጸሚያ በጀት ቅዱስ ሲኖዶስ አጽድቋል፡፡
12. በቤተ ክርስቲያኒቱ ማእከላዊ አስተዳደር አመራር ሰጭነት በልማት ዘርፍ ዙሪያ እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴ በበለጠ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ሁሉ ሊበረታታ የሚገባ ስለሆነ ሁሎችም አህጉረ ስብከት ለመልካም አስተዳደር መስፈን ዕንቅፋት የሆኑትን እያስወገዱ፤ የልማት አገልግሎትን በመዘርጋት እንዲሠሩ ምልአተ ጉባኤው ተስማምቷል፡፡
13. ሀገራችን ኢትዮጵያ ከበሽታ፣ ከድህነትና ከኋላ ቀርነት ወጥታ ሌላው ዓለም ወደደረሰበት ለመድረስ የምትችለው፣ ማንኛውም ወገን ተቻችሎና ተከባብሮ ለሰላምና ለልማት ሲነሣሣ ስለሆነ፣ ይኸው ታውቆ ሁሉም ኅብረተሰብ የበኩሉን ድርሻ ይወጣ ዘንድ ቤተ ክርስቲያናችን መልእክቷን ታስተላልፋለች፡፡
14. እንደኛ እምነት ሀገራችን ኢትዮጵያ የሥራን ክቡርነት የተረዳና እግዚአብሔርን መፍራት የጥበብ መጀመሪያ መሆኑን የተገነዘበው ወጣቱ ትውልድ ከሚፈጽመው መንፈሳዊና ማኅበራዊ ተግባር መረዳት ይቻላል፡፡ ከዚህ አንጻር ወጣቱ ትውልድ የሥነ አእምሮ ብቃቱን በማሳደግ፤ ሥራን የመፍጠር ክሂሎቱን ማረጋገጥ ያስችለው ዘንድ ቤተ ክርስቲያናችን ምክርዋን ታስተላልፋለች፡፡
15. የቤተ ክርስቲያኒቱ መሠረታዊ ተግባርና ተልእኮ ስብከተ ወንጌልን ማስፋፋት መሆኑ ይታወቃል፤ ጉባኤው በዚሁ ጉዳይ ላይ በስፋት ተነጋግሮ ሰባኪያነ ወንጌል በመንፈሳዊ ዕውቀታቸው እንዲጎለምሱ ተፈላጊው ሥልጠና እየተደረገላቸው እንዲሰብኩና እንዲያስተምሩ አስፈላጊው ድጋፍ ሁሉ እንዲደረግ ጉባኤው ወስኗል፡፡
16. በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በግብጽ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መካከል የቆየው ስምምነትና አንድነት ወደፊትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ተስማምቷል፡፡
17. በሀገራችን ኢትዮጵያ የዜጎችን ኋላ ቀር አኗኗር ለመለወጥ ዜጎች ሁሉ በእኩልነት ተሳስበው የሚኖሩበትን እድገት ማምጣት እንዲቻል በመንግሥትና በዜጎች ሁሉ እየተደረገ ያለው ጥረት ከፍተኛ ውጤትን እያስገኘ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በይቀጥላልም በልማቱ አቅጣጫ የሕዳሴያችንንም ግድብ ከፍጻሜ ለማድረስ በሚደረገው ርብርቦሽ የሀገራችንን የተፈጥሮ ሀብትና ጸጋ በማስጠበቅ ሕዝባችንን በማትጋት ቤተ ክርስቲያናችን የበኩሏን ሁሉ እንድታደርግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
18. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአገልግሎት አድማስን በማስፋፋት ኢትዮጵያውያን ባሉበት በተለያዩ የውጭ አገራት ቤተ ክርስቲያን እያቋቋመች ዜጐቿን እንደምታስተምርና እንደምታጽናና የሚታወቅ ነው፡፡ አሁንም ይህንኑ ማኅበራዊና መንፈሳዊ ተልእኮዋን ማስፋት እንዲቻል ቤተ ክርስቲያን እንዲቋቋም በሚል ጥያቄ ላቀረቡ ኢትዮጵያውያን አማንያን በጃፓንና በኮሪያ አዳዲስ አብያተ ክርስቲያናት እንዲቋቋሙ፣ መምህራንም እንዲላኩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
19. በውጭ አገር ከሚኖሩ አባቶች ጋር ተይዞ የነበረው የሰላም ድርድር ቤተ ክርስቲያናችን ምንጊዜም ቢሆን የምትፈልገውና በዚሁም ላይ አጥብቃ ስትሠራ የቆየችበት ጉዳይ መሆኑን ጉባኤው አውስቶ በቀጣይም በውጭ አገር ከሚገኙ አባቶች በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የሰላሙ ሂደት እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
20. ከጥቅምት 8 – 11 ቀን 2008 ዓ.ም. በተካሄደው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ 34ኛ መደበኛ ስብሰባ በተላለፈው የጋራ የውሳኔ ሐሳብ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ ተነጋግሮ የውሳኔ ሐሳቡ የ2008 በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ ሆኖ በሁሉም አህጉረ ስብከት ተላልፎ በየደረጃው በሥራ እንዲተረጐም ተወስኗል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ አሜን፣

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32015-11-02 08:28:262024-12-07 08:32:25ጥቅምት 12 ቀን እስከ 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ... Link to: ታህሣሥ 28 ቀን 2008 ዓ.ም የበዓለ ልደት መልእከት፣ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ታህሣሥ 28 ቀን 2008 ዓ.ም የበዓለ ልደት መልእከት፣ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ታህሣሥ 28 ቀን 2008 ዓ.ም የበዓለ ልደት መልእከት፣...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top