• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ጥቅምት 12 ቀን 2014 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

October 22, 2021

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

ብፁዕ አቡነ ያሬድ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኀላፊ፣የአርሲ ሀገረ ስብከት እና የምሥራቅ ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ፣የሲዳማ ክልል፣ የጌዴኦ አማሮና ቡርጂ ዞኖች አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፥
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በሙሉ፤

በዚህ ሐዋርያዊ ጉባኤ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ተልእኮ እንድንወያይ በየጊዜው የሚሰበስበን እግዚአብሔር አምላካችን ከዚህ ዕለትና ሰዓት ስላደረሰን ምስጋና ለእርሱ እናቀርባለን፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትም ወደዚህ ዓመታዊ ዐቢይ ጉባኤ እንኳን ደና መጣችሁ።

“ዕቀብ ማፀንተከ ዘተወፈይከ ከመ ትስብክ ቃሎ ቀዊመከ
ቆመህ ቃሉን ትሰብክ ዘንድ የተቀበልከውን አደራ ጠብቅ”
1ኛ ጢሞ. 4፥14)፡፡
በሁሉም ዘንድ እንደሚታወቀው በዓለም ያለው ኀላፊነት ሁሉ መንፈሳዊውም ሆነ ሥጋዊው ያለ አደራ የሚሰጥ አይደለምይልቁኑም ለቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ አደራ ከሁሉም የላቀ እንደሆነ አንስተውም ምክንያቱም ከሰው ሳይሆን በቀጥታ ከእግዚአብሔር የተሰጠ አደራ ከመሆኑም በተጨማሪ በሰማይም ሆነ በምድር ገደብ የለሽ ኀላፊነት በመሆኑ ነው ሌላው ተልእኮ የምድሩን ብቻ ሆኖ ከዚያም በጂኦግራፊ ወይም በመልክዐ ምድር ወይም በድንበር ወይም በሥጋዊና ዓለማዊ ጉዳዮች የተገደበ ነው የቅዱስ ሲኖዶስ ተልእኮ ግን ከዚህ በእጅጉ የተለየ ነው በምድር ላይ ምንም ዐይነት ድንበርና ወሰን ስለሌለው ገደብ የለሽ ነው ምክንያቱም ራሱ አደራ ሰጪው አምላክ “ሑሩ ወመሀሩ ውስተ ኲሉ አጽናፈ ዓለም ወስብኩ ወንጌለ ለኲሉ ፍጥረት — ወደ ዓለም ዳርቻዎች ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ” በማለት አዞናልና ነው ተልእኮው ይህ ከሆነ ዘንድ ኀላፊነቱም በዚህ ልክ ተሰጥቶናል ማለት ነው የቅዱስ ሲኖዶስ አደራ በመንፈስ ላይ ብቻ ያተኰረ ሳይሆን ምእመናንን በነፍሳቸውም ሆነ በሥጋቸው በምልአት መጠበቅን የሚመለከት ነው ማለትም ተልእኮአችን የእግዚአብሔር ልጆች የሆኑት ምእመናን በምድርም ሆነ በሰማይ፣በሥጋም ሆነ በነፍስ ለጉዳት እንዳይጋለጡ መጠበቅ ነው ማለት ነው፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት
ንዋይ ሩይ የተባለው ቅዱስ ጳውሎስ ለደቀ መዝሙሩ ለጢሞቴዎስ በላከለት መልእክት የተሰጠንን አደራ እንዴት መወጣት እንዳለብን በሚገባ አስረድቶናል ይውም ተግቶ ቃሉን በመስበክ አደራችንን መጠበቅ እንዳለብን ነው ምክንያቱም ቅዱስ ሲኖዶስ ከእግዚአብሔር ቃል የበለጠ የሰውን ኅሊና የሚረታና የሚያሳምን ሌላ ኀይል የለውምና ነው ቤተ ክርስቲያን በሁለት ሺሕ ዓመታት ተልእኮዋ የሕዝቡንና የአሕዛቡን ሕሊና ማርካ፣ መንፈሱን አርክታ ከጎኗ በማሰለፍ ለእግዚአብሔር ማቅረብ የቻለችው በዚህ ቅዱስና ኀያል ቃል ነው በመሆኑም እኛም ሆን የዘመኑ ትውልድ ከቃሉ የበለጠ ሌላ ኀይል እንደሌለ በውል ተገንዝበን፣ ለዚህም አጽንዖት ሰጥተን በትጋት መሥራት ግዴታችን ይሆናልቅዱስ ቃሉን በትጋትና በጥራት፣ በተመሥጦና በብቃት እያስተማርን መሆናችንና አለመሆናችንን የሚመሰክረው በምድሩ ላይ ያለው ተጨባጭ ውጤት እንደሆነም ማስተዋል ይገባናል ምእመናን እየበዙ በአገልግሎታችንና በትምህርታችንም እየተደሰቱ ከሆነ፣ እውነትም ቃሉን በትክክል አሥርጸናል ሠርተናልም ማለት ነው ተቃራኒው ከሆነ ግን ገና ይቀረናል ማለት ነውቅዱስ ሲኖዶስ በዚህ ጉባኤ ማየት መገምገምና ተጨባጭ የማስተካከል ሥራ መሥራት ያለበት በዚህ ዙሪያ ነው፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት
መንፈሳዊም ሆነ ዓለማዊ ሥራ በአግባቡ ለማከናወን የሰላም መኖር እጅግ በጣም አስፈላጊ እንደሆነ ለጥያቄ የሚቀርብ አይደለም ሰላም ከሌለ ሃይማኖታዊ አገልግሎትና አስተምህሮም መቆሙና መቋረጡ አይቀሬ ነው ሰላም ሲጠፋ አማንያንም ሆኑ አብያተ ክርስቲያናት ጉዳት ላይ ይወድቃሉይህም በመሆኑ ዛሬ በሀገራችን በተከሠተው የሰላም መደፍረስ ምክንያት ከላይ የተጠቀሱት ጉዳቶች በቤተ ክርስቲያናችን ሊከሠቱ ችለዋል፡፡ ይህ አሳዛኝ ክሥተት በሃይማኖት በወገንና በሀገር ላይ እያደረሰ ያለው ከባድ ጉዳት እንዲያበቃ ወደ እግዚአብሔር መጸለይና መማፀን ይኖርብናልነገሮች ሁሉ ከእግዚአብሔር በታች እንጂ በላይ ስላይደሉ መፍትሔው እሱ እንዲያመጣልን ወደ እርሱ አጥብቀን መጸለይ ይኖርብናል ከዚህም ጋር በጦርነቱ የተጐዱ ወገኖች ተደራራቢ ችግር እንዳያጋጥማቸው ሕዝቡን በማስተባበር ልንረዳቸውና ልንደርስላቸው ይገባል፡፡
በመጨረሻም በቀኖና ቤተ ክርስቲያን በተደነገገው መሠረት በጥቅምት ወር በየዓመቱ በዐሥራ ሁለተኛው ቀን የሚካሄደው ዓመታዊው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጸሎት የተከፈተ መሆኑን በእግዚአብሔር ስም እናበሥራለን።

እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን፤
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ፤
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32021-10-22 10:13:202025-01-27 10:15:14ጥቅምት 12 ቀን 2014 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጥቅምት 8 ቀን 2014 ዓ.ም 40ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ Link to: ጥቅምት 8 ቀን 2014 ዓ.ም 40ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ ጥቅምት 8 ቀን 2014 ዓ.ም 40ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ... Link to: ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 18 ቀን 2014 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ Link to: ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 18 ቀን 2014 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 18 ቀን 2014 ዓ.ም የተካሄደው...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top