• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ነሐሴ 11 ቀን 2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ሶማሌ፣ በባሌ፣ በሻሸመኔ፣ በጣና በለስና በሌሎችም አካባቢዎች ተፈጽሞአል በተባለውን የሰው መግደልና መፈናቀል እንዲቆም ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሰጥተዋል

August 17, 2018

ነሐሴ 11 ቀን 2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ሶማሌ፣ በባሌ፣ በሻሸመኔ፣ በጣና በለስና በሌሎችም አካባቢዎች ተፈጽሞአል በተባለውን የሰው መግደልና መፈናቀል እንዲቆም ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሰጥተዋል፣ ሲኖዶሱ በኢትዮጵያ ሶማሌ ለተፈናቀሉ ወገኖቻችን ከጠቅላይ ቤተ ክህነት 4 ሚሊዮን ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት 4 ሚሊዮን ብር ርዳታ እንዲሰጥ የተወሰነውን ቅዱስነታቸው ገልጸዋል፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤
በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትኖሩ፣ የተወደዳችሁና የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ሆይ!!

ሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅድመ ታሪክ ዘመን አንሥቶ ህልውናዋ፣ ታሪክዋ፣ ገናናነትዋ ታላቅነትዋና ሥልጣኔዋ በዓለም ዘንድ የታወቀ ታላቅና አኵሪ ሀገር ናት፤ ለታላቅነትዋ ዐቢይ አስተዋፅኦ ካበረከቱት መካከል በፈሪሀ እግዚአብሔርና በአምልኮተ እግዚአብሔር የተገነባ፣ ስለ ሃይማኖቱና ስለ አንድነቱ ፍንክች ሳይል በአንድነትና በጽናት የቆመ ሕዝብ ያላት መሆኑ ነው፡፡ በዚህ የሃይማኖት ሥርጸት የዜጎች የማይበጠስ አንድነትና ማኅበራዊ መስተጋብር ጸጋ ሀገሪቱ ከውጭ ወራሪዎች የሚሰነዘርባትን ማንኛውንም ጥቃት በሚገባ እየመከተች እስካሁን በኀያልነት ዘልቃለች፡፡

በዚህም የዓለም ሁሉ ጸሐፍትና ምሁራን ብቸኛ የሆነ አንጸባራቂ ታሪኳን ማንነትዋንና ነፃነትዋን በደማቅ ቀለም ጽፈውላታል፣ በቀላሉ ተዝቆና ተተንትኖ የማያልቅ ሃይማኖታዊና ሀገራዊ ታሪኳ በዓለምና በአፍሪካ ጎልቶ ሊወጣ የቻለው ሕዝቦቿ በሃይማኖት፣ በዘር፣ በቀለም፣ በመልከዐ ምድር፣ በባህልና በጥቃቅን ምክንያቶች ለሚፈጠሩ ልዩነቶች ቦታ ሳይሰጡ ዘላቂና የጋራ ጥቅማቸውን ለሚያረጋግጥ ሀገራዊ አንድነት ከማንም በፊት ቅድሚያ ሰጥተው እንደ ችቦና እንደ ነዶ አንድ ላይ በመቆማቸው እንደሆነ ታሪካችን አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ በተለይም በሃያ አንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሀገራችን ኢትዮጵያ ለምሥራቅ አፍሪካ አልፎም ለመላው አፍሪካና ለመላው የዓለም ጥቍር ሕዝቦች ተምሳሌት የሚሆን አንጻባራቂ የልማት፣ የአንድነትና የመልካም አስተዳዳር ስኬት ታረጋግጣለች ብሎ የዓለም ሕዝብ ተስፋ በጣለባት ወቅት፣ ዜጎች ለታሪካቸው፣ ለባህላቸውና ለሃይማኖታቸው የማይመጥን ሰብእና እንደዚሁም በዓለም ሕዝብ ፊት ኀፍረትና ፀፀት የሚያስከትል ተግባር እንዳይፈጽሙ በእጅጉ መጠንቀቅ አለባቸው፤

እንደሚታወቀው ሁሉ በመንፈሳዊው ዓለም ካልሆነ በቀር እኩያት ፍትወታት ባየሉበት በዚህ ዓለም እንከን የለሽ ሥራና ሠሪ ይኖራል ተብሎ አይጠበቅም፤ በመሆኑም ስላለፈው እንከን ስናቀነቅን የወደፊቱ ዕድል እንዳያመልጠን ሁሉንም ነገር በይቅርታና በፍቅር ማለፍ አማራጭ የሌለው ጥበብ እንደሆነ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በውል ሊገነዘቡት ይገባል፣ሀገራችን ኢትዮጵያ በጥቍሮች ዓለም፣ በአፍሪካና ይልቁንም በምሥራቅ አፍሪካ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሆና እንድትታይ ያደረጋት ምሥጢር የሃይማኖቷ ጸጋና የሕዝቦችዋ አንድነት እንደሆነ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በተለይም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ወጣት ልጆቻችን ከልብ እንድትገነዘቡት አጥብቀን እንመክራለን፤

ታላቅና ገናና የሆነች ኢትዮጵያ በአንድነቷ እንደ ታፈረች፣ እንደተከበረችና ኀያል እንደሆነች እንደጥንቱ እንድትቀጥል የማይፈልግ ኢትዮጵያዊ እንደሌለ በእርግጠኝነት እናውቃለን፡፡ ነገር ግን መንገዱን ስተን ወደ ገደል እንዳንገባ በማስተዋልና በአርቆ አሳቢነት መጓዝ ይገባናል፤ በዚህ ዙሪያ የሃይማኖት መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራንና አርቲስቶች ያለመታከት ሌት ተቀን መሥራት ይኖርባችኋል፤ ወጣት ልጆቻችንም በማኅበራዊ ሚዲያ ቅስቀሳ፣ በአፍራሽ የቅንብር ወሬና በስሜት ሳትሸነፉ የነገዋን ኢትዮጵያ ብሩህ ተስፋ ከወዲሁ በመመልከት ከሁሉም በላይ ለሀገር አንድነትና ለዜጎች ደኅንነት በጽናት እንድትቆሙ በሚወዳችሁና በምትወዱት በእግዚአብሔር ስም አጥብቀን አደራ እንላችኋለን፡፡

የተወደዳችሁና የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች!! ለዚህች ሀገር መነሻም መገስገሻም ሆና ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በእኩልነት እያስተናገደች የኖረችና ያለች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እንደሆነች ማንም ኢትዮጵያዊ አይስተውም፣ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናችን ለሀገሪቱ የሃይማኖት፣ የባህል፣ የቅርስ፣ የዕውቀት፣ የሥነ ጽሑፍ፣ የሥነ ጥበብ፣ የመቻቻልና የአብሮነት ጒልላት የሆነች፣ በማንም ይሁን በማን ላይ እጅዋን ጭና የማታውቅ፣ ሁሉንም በሰላምና በፍቅር እንደዚሁም በእናትነት መንፈስ የምትመለከት ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ ይሁን እንጂ በአሁኑ ጊዜ በእርስዋ ላይ እየተሠነዘረ ያለው አሳፋሪ፣ ዘግናኝና አሠቃቂ ድርጊት የናት ጡት ነካሽ የሚያስብል፣ ሊደረግ ቀርቶ ሊታሰብ የማይችል፣ በእግዚአብሔር አምናለሁ የሚል ቀርቶ ሃይማኖት የለሽ ፍጡር የማይፈጽመው ድርጊት በኢትዮጵያ ሶማሌ፣ በባሌ፣ በሻሸመኔ፣ በጣና በለስና በሌሎችም አካባቢዎች ተፈጽሞአል፡፡

ይህ ዘግናኝና አሳፋሪ ድርጊት ቅዱስ ሲኖዶስን ብቻ ሳይሆን መላ ኢትዮጵያውያንን ያሸማቀቀ ድርጊት ነው፤ በዚህ አሳዛኝና አሠቃቂ ድርጊት ለጊዜው የታወቁት ዘጠኝ አብያተ ክርስቲያናት ከነሙሉ ንብረታቸውና ሀብታቸው በቃጠሎና በዝርፊያ ወድመዋል፤ የሀገረ ስብከቱ መንበረ ጵጵስና፣ ጽ/ቤቱና መኪናው፣ እንደዚሁም የቤተክርስቲያኗ ት/ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል፤ ንብረታቸውም ተዘርፈዋል፡፡ ለጊዜው የታወቁ አምስት ካህናት በአሠቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል፣ ሰባት ካህናትም በጽኑ ተደብድበው ሞተዋል ከተባሉ በኋላ ተርፈው በሕክምና እየተረዱ ይገኛሉ፤ ገና ቊጥራቸው ያልታወቀ ምእመናንም በተመሳሳይ ሁኔታ ተገድዋል፣ ተደብድበዋልም ሀብታቸውና ንብረታቸውም ተዘርፎአል፡፡ ይህ ኢሰብኣዊ የሆነ አሠቃቂ የጭካኔ ድርጊት በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በሌሎች አብያተ ሃይማኖትም እንደተፈጸመ ለማወቅ ተችሎአል፡፡ በመሆኑም በቤተ ክርስቲያንና በዜጎች ላይ የደረሰው ጉዳት እጅግ ከባድ ከመሆኑ አንጻር ሁኔታውን በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ለወገን ደራሽ ወገን ነውና በተቻለው ሁሉ የተቸገሩትን፣ የሚላስ፣ የሚቀመስ እንዲሁም የሚለበስ ያጡትን ወገኖችን ለመርዳት የበኩሉን በማድረግ እንዲረባረብ፣ የፈረሱትንና የተቃጠሉትን አብያተ ክርስቲያናት እንደገና መልሶ ለመሥራት በሚደረገው ርብርብ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ቤተ ክርስቲያናችን በእግዚአብሔር ስም ጥሪዋን ታስተላልፋለች፡፡

በመጨረሻም፡ የዜጎች ደኅንነት፣ የሀገር ሰላምና አንድነት የሚጠበቀው ገደብ የለሽ መብትና ነፃነት በመስጠት ብቻ ሳይሆን የሕግን የበላይነት በማስፈንና ሥነ ሥርዐትን በማስጠበቅ እንደሆነ ጥርጥር የለውም፤ ይሁንና መንግሥት ለብሔራዊ መግባባት ሲል የሚከተለው ከመጠን ያለፈ ትዕግሥት የሀገሪቷን አንድነትና የዜጎችዋን ደኅንነት በከባድ ሁኔታ እየሸረሸረ ስለሆነ ሳይውል ሳያድር የዜጎችን የመኖር ዋስትና፣ የሃይማኖትን ልዕልና በሕጉ መሠረት በመጠበቅ ፀጥታውን እንዲያስከብር፣ ኦርቶዶሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በአጽንዖት ትማፀናለች፤ እንደዚሁም ተፎካካሪ የፖለቲካ ኀይሎችና ሕዝቡም ከሁሉ በፊት ለሀገር አንድነትና ለዜጎች ደኅንነት ቅድሚያ ሰጥታችሁ እንድትሠሩ፣ ወጣት ልጆቻችንም በስሜት ተገፋፍታችሁ በወገን ላይ መጨከንን ከዛሬ ጀምሮ እርም ብላችሁ እንድታቆሙ፣ መንግሥት፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የሚሏችሁን ብቻ እየሰማችሁ ሀገር የምታድግበትን አንድነትዋ የሚጠበቅበትንና ሰላምዋ የሚጠናከርበትን ሥራ ብቻ ለመሥራት በማስተዋል እንድትተጉ አባታዊ መልእክታችንን በድጋሚ በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32018-08-17 09:15:022025-01-27 09:16:43ነሐሴ 11 ቀን 2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ሶማሌ፣ በባሌ፣ በሻሸመኔ፣ በጣና በለስና በሌሎችም አካባቢዎች ተፈጽሞአል በተባለውን የሰው መግደልና መፈናቀል እንዲቆም ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሰጥተዋል
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ነሐሴ 1 ቀን 2010 ዓ.ም. የጾመ ፍልሰታ ሙሉ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ነሐሴ 1 ቀን 2010 ዓ.ም. የጾመ ፍልሰታ ሙሉ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ነሐሴ 1 ቀን 2010 ዓ.ም. የጾመ ፍልሰታ ሙሉ ቃለ ምዕዳንና... Link to: የመስከረም 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ዘመን መለወጫ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: የመስከረም 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ዘመን መለወጫ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የመስከረም 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ዘመን መለወጫ በዓል ቃለ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top