• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ሚያዝያ 24 ቀን 2010 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

May 2, 2018

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ብፁዓን ኤጲስ ቆጶሳት፣ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በሙሉ
እግዚአብሔር አምላካችን ለዚህ ዓመታዊ የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስላደረሰን እንደዚሁም ከየሀገረ ስብከታችን አሰባስቦ አንድ ላይ ስላገናኘን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን፡፡

“ዘይሁብ መርሐ ርቱዐ ለቤተ ክርስቲያን” ለቤተ ክርስቲያን የተስተካከለ መርሕን የሚሰጥ እግዚአብሔር አምላክ ነው› (መጽሐፈ ኪዳን)፡፡

ሁላችንም እንደምንገነዘበው መርሕ ወይም ሕግ ካለ ባለቤት አለ፤ ሕጉን የሚያስፈጽም አገልጋይም አለ፤ የሕጉ ባለቤት ቤተ ክርስቲያንን በደሙ የመሠረተ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰማያዊ አምላክ እንደመሆኑ መጠን ለቤተ ክርስቲያን የሰጠው መርሕም ሰማያዊ ነው፡፡ ይህም ማለት የመጨረሻ መዳረሻው ሰማየ ሰማያት መሆኑን የሚያመለክተን እንጂ በጌታችን የተሰጠው መርሕ መነሻው በምድር ሳሉ የሚተገበር ነው፡፡ መርሑ በምድር ላይ መተግበር ስለነበረበትም ትግበራውን ሊከታተሉና ሊያስፈጽሙ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የውክልና ሥልጣን በሀብተ ክህነት ተሰጥቷል፡፡

በጌታችን የተሰጠው መርሕ ቅዱስ ወንጌል እንደሆነ ሁላችንም የምናውቀው ነው፤ የቅዱስ ወንጌል መልእክትም በአጭር አባባል ሲገለጽ ሰውን አስተምሩ፣ ሰውን ጠብቁ፣ ሰውን ለድኅነት አብቁ የሚል ነው፤ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትም ውክልና የተሰጠን ይህንን መርሕ ለማስፈጸም ነው፡፡ ይህንም ስንፈጽም ብቻችን እንዳይደለን እርሱ ባለቤቱ ቀጥሎ ቀጥሎ በሚደረግ ተአምርና ሙሉ ጥበቃ ቃሉን እያጸና በሥራችን ሁሉ ዘወትር ከኛ ጋር እንደሆነ በማይታበል ቃሉ አረጋግጦልናል፡፡

በዚህ ሕያውና አምላካዊ ቃል ኪዳን መሠረት ቤተ ክርስቲያን ቃሉን ለዓለም ሁሉ ማድረስ ችላለች፡፡ በሁሉም ያለች፣ ሐዋርያዊት፣ አንዲትና ቅድስት የሆነች ቤተ ክርስቲያናችንም በእግዚአብሔር ፈቃድ ዛሬ እግሯ ያልረገጠው ክፍለ ዓለም የለም፤ ከዚህ አኳያ ቤተ ክርስቲያናችን በአሁኑ ጊዜ ብሔራዊት ብቻ ሳትሆን ዓለም ዐቀፋዊት ሆና የወጣችበት ዘመን ሆኖ ይገኛል፡፡ እግዚአብሔር በልዩ ጥበቡ ይህንን የሐዋርያነት ጸጋ ስላደለን ቤተ ክርስቲያናችን በገባችበትና እግር በተከለችበት ሁሉ የተደራጀ የተጠናከረና በስልታዊ ጥበብ የታቀደ ሥራን በመሥራት ይበልጥ እንዲሰፋ ማድረግ ከዚህ ዐቢይ ጉባኤ ቀና ትብብርና ተነሣሽነት ያስፈልጋል፡፡

ከጌታችን በተሰጠው መርሕ መሠረት ቤተ ክርስቲያናችን ምእመናንን ለማስተማር፣ ለመጠበቅና ለድኅነት ለማብቃት ከሁለት ሺሕ ዓመታት በላይ ባደረገችው ተጋድሎ ስፍር ቍጥር የሌላቸው አማንያንንና ቅዱሳንን ለመንግሥተ እግዚአብሔር ማብቃቷ ለጥያቄ የሚቀርብ አይደለም፡፡ አሁን ባለንበት የፈተና ዘመንም ቤተ ክርስቲያናችን ምእመናንን በየደረጃቸው በቃለ ዐዋዲ አደራጅታ እያስተማረች፣ እየጠበቀችና ለመንግሥተ እግዚአብሔር እያበቃች ትገኛለች፡፡ ከሃያኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በቃለ ዐዋዲ አደረጃጀት ባደረገችው የሥራ እንቅስቃሴ ልምድ ሙሉ በሙሉ ወደተሻለ የጥበቃ ሥራ ሊያሸጋግራት የሚችል ዐቅም መፍጠር እንደምትችል በተጨባጭ አይተናል፤ ምእመናን በአጠቃላይ በተለይም ወጣቶች ቤተ ክርስቲያንን ለመደገፍና ለመጠበቅ ብሎም የመንግሥተ እግዚአብሔርን ዜጎች ለመሆን የሚያደርጉት እሽቅድድም እጅግ አስደሳች ሆኖ ተገኝቷል፡፡

ይህም የቃለ ዐዋዲ አደረጃጀት ያስገኘው ጸጋ እንደሆነ የማንስተው ነው፤ ቃለ ዐዋዲው ያላቀፈው የክርስቲያን ማኅበረ ሰብ በአሁኑ ጊዜ የለም፤ ካለማወቅ የሚቀር ባይጠፋም ዕድሉ ግን ለሁሉም ክፍት አድርጎ ሰጥቷል፤ ስለሆነም የቃለ ዐዋዲ መዋቅር የቤተ ክርስቲያናችን የአንድነቷ፣ የሀብቷና የሃይማኖቷ መጠበቂያና የምእመናን ዋስትና ስለሆነ ልንጠብቀው ይገባል፡፡ ቀረ የሚባል ካለም በጥናት ላይ በተመሠረተ አሠራር በቃለ ዐዋዲው እያካተቱ ከመሥራት ውጭ የተሻለ ጠቃሚ ነገር አይኖርም፡፡

በቤተ ክርስቲያናችን የሚከናወነው መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አሠራር እንደማንኛውም ሰብኣዊ ሥራ የራሱ የሆነ ጥንካሬና ድክመት እንዳለው ሁላችንም እንገነዘባለን፤ ቀድሞውኑም ይህ ሊኖር እንደሚችል ታሳቢ ተደርጎ ነው የቀደሙት ቅዱሳን አበው በዓመት ሁለት ጊዜ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ እንዲኖር በቀኖና የደነገጉት፤ ስለሆነም የመሰብሰባችን ዐቢይ ዓላማ የቤተ ክርስቲያናችንን ጠቅላላ ሥራ በመገምገም ጥንካሬያችንን ይበልጥ አጎልብተን ለመቀጠል ድክመታችንን ደግሞ በፍጥነት አርመን ለሕዝበ ክርስቲያኑ የተሻለ አስተምህሮና የተጠናከረ ጥበቃ በማድረግ ለእግዚአብሔር መንግሥት ለማብቃት ነው፡፡ ከዚህ አኳያ ባለፉት ወራት የነበረው የሀገራችን ሁኔታ ፈታኝና ከሃይማኖት አባቶች ብዙ ሥራ መሥራትን የሚጠይቅ እንደሆነ አስተውለናል፤ ይሁንና አሁን ባለው ሁኔታ አንጻራዊ መረጋጋት የሚታይበት ጊዜ እግዚአብሔር በቸርነቱ ሰጥቶናል፡፡ ይህም በሕዝቡ በተለይም በወጣቱ ትውልድ ይበልጥ ሥርጸት እንዲያገኝ ከእኛ ከሃይማኖት አባቶች ባለመታከት ቀን ከሌሊት ተግቶ የማስተማርና የመጠበቅ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል፡፡

ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎትና ለሕዝብ ጥበቃ ከአምላክ ሥልጣነ ክህነትን የተቀበሉ ሁሉ ሀገርን ከቤተ ክርስቲያን፣ ቤተ ክርስቲያንን ከሀገር ነጥለው ማየት የለባቸውም፤ ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን የምትኖረው በሀገር ውስጥ ነው፤ ጠንካራና ዘላቂ እምነቷን የምታስጠብቀውም ሀገር አንድ ስትሆን ነው፤ የሀገር አንድነትና የሕዝቦች ስምምነት ከሌለ የቤተ ክርስቲያን አንድነትም አይኖርም፤ ስለዚህ እኛ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ለሀገር አንድነት የሚበጅ ሥራን በመሥራትና በማስተማር ተምሳሌትና አርኣያነት ያለው ሥራ ለመሥራት መጣር አለብን፤ ዓለሙ በጮኸ ቊጥር የምንጮኽ ሳይሆን ለሃይማኖታችን፣ ለሕዝባችን፣ ለሀገራችንና ለአንድነታችን የሚበጀውን ብቻ በመከተል ሕዝቡን መምራት ይጠበቅብናል፡፡

ዛሬ ዓለማችን ለመንግሥተ እግዚአብሔር ዜጎች እጅግም የማትመች እየሆነች መምጣቷ በግልጽ የሚታይ ነው፤ አስተሳሰቦች በፍጥነት እየተቀያየሩ፤ የሥነ ምግባር ዕሴቶችም በፍጥነት እየተሸረሸሩ፤ አማንያን ወዲያና ወዲህ እየባዘኑ የሚታይበት ጊዜ ነው፤ ከዚህ አኳያ ከተወሰኑ ጊዜያት በኋላ አማንያን ምን ዐይነት ቁመና ይኖራቸው ይሆን; የሚለው ጥያቄ እየገፋ ነው፤ ይህ ፈተና ምዕራባውያንን ባዶአቸውን እያስቀራቸው እንደሆነም በግልጽ እየተሰማ ነው፤ እስካሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከሌላው ሁሉ የኦርቶዶክሱ ዓለም በጥንካሬ እንደሚገኝ ሁኔታዎች ያሳያሉ፤ ይህም በደምብ ከተሠራበት የኦርቶዶክስ ሃይማኖታዊ አስተምህሮና ቀኖና ፈተናን የመቋቋም ዐቅሙ ከፍ ያለ መሆኑን ስናይ ተስፋችን የላቀ እንዲሆን አድርጎታል፤ በመሆኑም ከኦርቶዶክሱ ዓለም በተለይም ከአኃት አብያተ ክርስቲያናት ጋር ያለውን ሃይማኖታዊ አንድነት እንደተጠበቀ ሆኖ ከራሺያ ቤተ ክርስቲያን ጋር በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ፣ በሰላምና በልማት ተግባራት እንደዚሁም በሁለንተና የሥራ መስክ ሥልጠና በጋራ መሥራት እንደሚያስፈልገን ተገንዝበናል፡፡

በመሆኑም በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት የልኡካን ልውውጥ በሁለቱም አብያተ ክርስቲያናት ተካሂደዋል፤ በቀጣይም በከፍተኛ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ተጨማሪ ጒብኝቶች በሁለቱም ሀገሮች ለማድረግና ግንኙነቱን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ በሰፊው እየሠራን ነው፤ ቅዱስ ሲኖዶስም ድጋፉንና ትብብሩን እንዲያክልበት በዚህ አጋጣሚ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡

በመጨረሻም፡ ይህ ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገር አንድነት የሚጠቅሙ መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን በዝርዝር በማየት በመገምገምና አቅጣጫ በማስቀመጥ ውጤታማና ሰላማዊ ጉባኤ እንዲሆን በመመኘትና በመጸለይ የ2010 ዓ.ም. የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ የተከፈተ መሆኑን እናበሥራለን፡፡

እግዚአብሔር አምላካችን ጉባኤያችንን ይባርክ፣ይቀድስ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32018-05-02 14:01:072024-12-10 14:02:46ሚያዝያ 24 ቀን 2010 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: መጋቢት 30 ቀን 2010 ዓ.ም. የትንሣኤ በዓል ሙሉ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: መጋቢት 30 ቀን 2010 ዓ.ም. የትንሣኤ በዓል ሙሉ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ መጋቢት 30 ቀን 2010 ዓ.ም. የትንሣኤ በዓል ሙሉ ቃለ... Link to: ከሚያዝያ 24 ቀን እስከ 29 ቀን 2010 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ Link to: ከሚያዝያ 24 ቀን እስከ 29 ቀን 2010 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ ከሚያዝያ 24 ቀን እስከ 29 ቀን 2010 ዓ.ም የተካሄደው...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top