• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ሚያዝያ 16 ቀን 2014 ዓ.ም ቅዱስነታቸው የትንሣኤ በዓል በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል

April 24, 2022

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤
የሀገራችን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
በሕመም ምክንያት በየጸበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤
እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ሁሉ፤

እንኳን ለ2014 ዓ.ም የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ፡፡

“ወይእኅዝዎ ለወልደ ዕጓለ እመሕያው ወይሰቅልዎ፣ ወይቀትልዎ ወአመ ሣልስት ዕለት ይትነሣእ፡- የሰውን ልጅ ይይዙታል፤ ይሰቅሉታል፤ ይገድሉታል፤ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል” (ማቴ.፳፮፥፪ ፤ ማር. ፰፥ ፴፩)።
በሁሉም ዘንድ እንደሚታወቅ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ሲገለጥ እስከ ሞት የሚያደርስ መከራ እንደሚቀበል፣ ከመከራ በኋላም ሞትን ድል አድርጎ እንደሚነሣ ኦሪትም ነቢያትም፣ መዝሙራትም በተለያየ አገላለጽ አሳውቀዋል፡፡ ቀደምት ሊቃውንትም ይህንን እውነታ ሲያረጋግጡ “ኦሪት ወነቢያት ሰበኩ በክርስቶስ፤ ማለትም ኦሪትና ነቢያት ክርስቶስን ሰበኩ” በማለት አመሥጥረዋል፡፡
እሱ ራሱም በምድረ እስራኤል እየተዘዋወረ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ሲያስተምር፣ በተነገረው ትንቢት መሠረት እንደሚያዝ፣ እንደሚሰቀልና እንደሚገደል፣ በሦስተኛው ቀን ግን እንደሚነሣ ለደቀ መዛምርቱ ደጋግሞ አስረድቶአል፡፡ እንግዲህ እኛ ሰዎች ይህንን አምላካዊ ድርጊት ስናይ ለምን እንደዚህ መሆን አስፈለገ? ብለን እንጠይቅ ይሆናል፤ ቅዱስ መጽሐፍ ለዚህ ጥያቄ ግልጽና የማያሻማ መልስ አለው፡፡
ይኸውም ቅዱስ መጽሐፍ ዳር እስከ ዳር እንደ ኀብለ ሰረሰር እርስ በርስ እየተናበበ ሲያውጅ የሚገኘው እግዚአብሔር በክርስቶስ ቤዛነት ትዝምደ ሰብእን ለማዳን ቃል መግባቱን ነው፡፡ በመሆኑም ቅዱስ መጽሐፍ ለተጠየቀው ጥያቄ መልስ ሲሰጥ ክርስቶስ በመከራ እንዲያልፍ ያስፈለገበት ዋና ምክንያት በእግዚአብሔር ትክክለኛ ፍርድ ፊት ለኀጢአት ቅጣት በተጋለጡ ሰዎች ፈንታ ቤዛ ሆኖ በመሞት ሰዎችን ለማዳን ነው ይለናል፡፡
ከዚህ አኳያ ይህ አድራጎት እግዚአብሔር ሰውን ብቻ ሳይሆን በኀጢአት የተበከለውን ምልአተ ዓለም በሙሉ ንጹሕ በሆነ ደመ ክርስቶስ ለማንጻትና ለመቀደስ የመረጠው መለኮታዊ አሠራር መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ እንደ ፈቃዱም እንሆ ዛሬ ዓለምንና በውስጡ የሚገኙትን በሙሉ በደሙ አንጽቶአል፤ በዚህም አድራጎቱ በእርሱ በኩል ስለ ድኅነተ ዓለም ሊደረግና ሊከፈል የሚገባው የዕዳ ኀጢአት ካሳ ከፍሎአል፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት፤
እግዚአብሔር በሕግ ፈጥሮ፣ በሕግ የሚያስተዳድር አምላክ እንጂ ከኔ በላይ ማንም ስለሌለ እንደፈለግሁት ማድረግ እችላለሁ የማይል እውነተኛ ዳኛ መሆኑን በውል መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም ሕግ የሚጠይቀውን የኀጢአተኝነት ቅጣት የሚሸከም ወይም ኀላፊነት ወስዶ በኀጢአተኞች ፈንታ የሚቀጣ ሳይኖር ኀጢአተኛን ያለ ቅጣት አይተውም፤ ለዚህም ነው “በደለኛውን ከቶ የማያነፃ” በማለት የማይለወጥ ትክክለኛ ፍርዱን ያሳወቀው፡፡
ነገር ግን እግዚአብሔር በትክክል የሚፈርድ ዳኛ ብቻ ሳይሆን ምሕረትና ይቅርታ በማድረግም ርኅሩኅነቱን ደጋግሞ ያሳወቀ አምላክ ነው፡፡ ይህንን የአምላክ ምሕረትና ይቅርታ ተጠቃሚ ለመሆን እሱን ማመና ንስሓ መግባት ያስፈልጋል፡፡
በመሆኑም መሓሪው አምላካችን በአንድ በኩል ትክክለኛው ፍርዱን ሳይተው በሌላው በኩል ደግሞ ሕግ የሚጠይቀውን ቅጣት ራሱ በመቀበል በኀጢአታችን ከመጣብን የኀጢአት ቅጣት ማለትም ከዘለዓለማዊ ሞተ ነፍስ ነፃ አደረገን፡፡
ለዚህም ነው “ክርስቶስ መድኀኒነ መጽአ ወሐመ በእንቲኣነ ወበሕማማቲሁ አድኀነነ፤ መድኀኒታችን ክርስቶስ መጣ፤ በኛ ፈንታም መከራ መስቀልን ተቀበለ፤ በመስቀል ላይ በተቀበለው መከራም አዳነን” ተብሎ የተነገረን፡፡ ከዚህ አንጻር በቤዛነት የተመሠረተ የማዳን አሠራር በሕግ ፊት ተቀባይነት ያለው በመሆኑ የእርሱ ቤዛችን ሆኖ መሞት እኛን ከሞተ ነፍስ ማዳን ችሎአል፡፡
በዚህ ምክንያት በሱ መሰቀል ኀጢአትንና ሞትን ማሸነፍ ስለቻልን ቅዱስ ጳውሎስ “ወለእግዚአብሔር አኰቴት ዘወሀበነ ንማእ በእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት ሞተ ነፍስን ድል እንድንነሣ ላደረገን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን” በማለት በተመሥጦና በአድናቆት የታጀበ ምስጋና ያቀርባል፡፡
ይሁን እንጂ በክርስቶስ ደም መዳን እንችል ዘንድ ማድረግ የሚገባን እንዳለ መድኀኒታችን በቅዱስ ወንጌል በሚገባ ነግሮናል፤ ይኸውም በልጁ ያመነ የዘለዓለም ሕይወት ያገኛል የሚለው ገዢ ቃል ነው፡፡ ከዚህ አኳያ የሰው ልጅ ሁሉ ከኀጢአት ቅጣት አምልጦ ይህንን የመዳን ድል ለመቀዳጀት ዋናው ቍልፍ ተግባር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመንና ንስሓ መግባት ነው፤
እሱን በምልአት የማመኑ ነገር ከተሟላ ሌላው ሁሉ እሱ ያስተማረውን በምልአት በመቀበል የሚሆን ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታችን ያስተማረው ትምህርት በሙሉ እውነት እንደ ሆነ የክርስቶስ ትንሣኤ አረጋግጦአልና ነው፡፡ ክርስቶስ ሲነሣ ብቻውን የተነሣ አይደለም፤ ያስተማረው ትምህርትም ሆነ የሠራው ሥራ ሁሉ እንደዚሁም ስለ እርሱ የተነገረው ትንቢት በሙሉ አብሮት ተነሥቶአል፡፡ ምክንያቱም ትንሣኤው የትምህርቱ እውነተኛነት ምስክር ነውና፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት።
ትንሣኤ ክርስቶስ ለእኛ ለክርስቲያኖች የሃይማኖታችን ሁለንተናዊ ሕይወት ነው፡፡ ትንሣኤው በምድራዊ ሕይወታችንም ሆነ በሰማያዊ ሕይወታችን የላቀ ትርጒም ያለው ነው፡፡ እኛ ክርስቲያኖች በምድራዊ ሕይወታችን ከግብረ ኀጢአት ርቀን፣ በበጎ ሥራ አሸብርቀን፣ በፍቅርና በአንድነት፣ በስምምነትና በመቻቻል፣ በመተዛዘንና በመተሳሰብ፣ በዕርቅና በሰላም እንድንኖርና የሞራል ትንሣኤ እንዲኖረን ያነሣሣናል፡፡
በመንፈሳዊ ሕይወታችን በኩል ደግሞ ከሞት በኋላ ያለውን ትንሣኤና የማያልቅ ዘለዓለማዊ ሕይወት በሩቅ እንድናይና በተስፋ ተሞልተን በመጽናናት እንድንኖር ያስችለናል፡፡ በመሆኑም ክርስቲያኖች የትንሣኤ ልጆች በመሆናችን ከማንም በላይ የላቀ የሞራል ልዕልና ሊኖረን ይገባናል፡፡
ደገኛው ትንሣኤያችንን በጌታችን ቀን እስክንቀዳጅ ድረስም ትንሣኤ ልቡናን በመነሣት የጨለማው ዓለም ብርሃናት ሆነን ልንመላለስ ይገባናል፡፡ የክርስቶስ ትንሣኤ ጥላቻንና መጠፋፋትን ያስወገደ፣ ሰላምን ያሰፈነ፣ ዕርቅን ያረጋገጠ ነው፡፡ እኛም በዓለ ትንሣኤውን ስናከብር የእርሱ ደቀ መዛሙርት ነንና ከኛ የሚጠበቀው ይኸው ዐይነት ክርስቶሳዊ ሕይወት ነው፡፡
በመጨረሻም፡ ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ መተባበር ለሁላችንም ክርስቲያኖች ሃይማኖታዊ ግዴታችን ነውና ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በትንሣኤው ዕለት ተርበውና ተጠምተው፣ ታርዘውና ተስፋ ቈርጠው መዋል ስለሌለባቸው በልዩ ልዩ ምክንያት መከራ ላይ ለሚገኙ ወገኖቻችን የሚያስፈልጋቸውን በማቅረብ ፋሲካውን አብረናቸው እንድናከብር ነው፡፡
እንደዚሁም የሰላምና የፍቅር፣ የዕርቅና የይቅርታ ኀይሎች ሆነን በመመላለስ ሀገራችንን ከፈተና ሕዝባችንን ከሰቆቃው እንድንታደግ ለኢትዮጵያውያን ሁሉ አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡
መልካም የትንሣኤ በዓል ያድርግልን ፤
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክልን ይቀድስልን!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32022-04-24 14:21:472025-01-28 14:23:19ሚያዝያ 16 ቀን 2014 ዓ.ም ቅዱስነታቸው የትንሣኤ በዓል በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል Link to: የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን... Link to: ግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top