• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

መስከረም 1 ቀን 2012 ዓ.ም. የዘመን መለወጫ በዓልን ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

September 12, 2019

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣

ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣

የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣

በሕመም ምክንያት በየጸበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጰያውያንና ኢትዮጵያውያት፡፤

የዘመናትና የዓመታት ባለቤት የሆነው እግዚአብሔር አምላካችን የሁለት ሺሕ ዐሥራ አንድ ዓመተ ምሕረት ዘመነ ሉቃስን በሰላም አስፈጽሞ ወደ ሁለት ሺሕ ዐሥራ ሁለት ዓመተ ምሕረት ዘመነ ዮሐንስ እንኳን በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!

“አመ ርእሰ ሳብዕ ወርኅ ግበሩ መጥቅዐ፤ በሰባተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ዕረፍት፣ በመለከት ድምፅ መታሰቢያ የተቀደሰ ጉባኤ ይሁንላችሁ” (ዘሌ. 23፥24)፡፡

የኢትዮጵያ የዘመን አቈጣጠር ሥር መሠረቱ ቀመረ አዳም፣ ቀመረ ኖኅ እንደሆነ ቅዱስ መጽሐፍ ያስረዳል፡፡ ይህም አቈጣጠር እስከ ዘመነ ሙሴ በመካከለኛው ምሥራቅ ሕዝቦች ሁሉ ጥቅም ላይ የዋለ ነበረ፡፡ በሊቀ ነቢያት ሙሴ ዘመን ግን በእግዚአብሔር ኀይል የሕዝበ እስራኤል ከግብጽ ባርነት መውጣትና ነፃነት ማግኘት ጋር በተያያዘ ወርኀ ሚያዝያ የወር መጀመሪያ እንዲሆን እግዚአብሔር ትእዛዝ መስጠቱ በቅዱስ መጽሐፍ ተመዝግቦአል፡፡ ይሁንና የወር መጀመሪያ እንጂ የዓመት መጀመሪያ ከመስከረም እንዳልተፋለሰ ‹‹በሰባተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን በድምፀ መለከት የተቀደሰ ጉባኤ ይሁንላችሁ›› ተብሎ ከእግዚአብሔር ለሙሴ በተሰጠው ትእዛዝ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ሕዝበ እስራኤል ዛሬም ድረስ በጨረቃ አቈጣጠር ቢሆንም የዘመን መለወጫ ዐውደ ዓመታቸውን የሚያከብሩት መስከረም ላይ ነው፡፡ ወደ ኢትዮጵያ ሀገራችን ቀመረ ዘመን አጠቃቀም የተመለከትን እንደሆነ የኖኅ አቈጣጠርን በትክክል የተከተለ ሆኖ ይገኛል፡፡ ይኸውም የቀኑም የወሩም የዓመቱም መጀመሪያ አንድ ላይ መስከረም አንድ ቀን መሆኑ ነው፤ የኖኅ ቀመር የሚቈጠረው በፀሓይ አቈጣጠር ሆኖ ከጳጉሜን በቀር ሁሉም ወሮች በሠላሳ ቀናት የተመደቡ መሆናቸውን መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹በሁለተኛው ወር፤ በዐሥራ ሰባተኛው ቀን የጥፋት ውኃ መዝነብ መጀመሩን ገልጾ፣ ከመቶ ኃምሣ ቀን በኋላ ደግሞ በመጀመሪያው ወር በመጀመሪያው ቀን ውኃው ከምድር ላይ ደረቀ›› ይላል፤ ይህም በጥቅል ሲገለጽ አምስት ወር እንደሆነ ያሳያል፤ በዚህ ስሌት መሠረት ወሮቹ በሠላሳ ቀናት የተመደቡ መሆናቸውን በግልጽ ያመለክታል ፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ ሀገራችን እንዲህ ያለውን በእግዚአብሔር ትእዛዝና በአበው ትውፊት ከጥንት ከዘመነ አዳም ወኖኅ ጀምሮ የነበረውን የዘመን መለወጫ ርእሰ ዐውደ ዓመት እስከ ዛሬ ድረስ ጠብቃ ማቈየቷ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን ለመላው ዓለም የሚያኮራ ነው፡፡

ዛሬ የምንጠቀምበት የዘመን መለወጫ ርእሰ ዐውደ ዓመት ጥንት የብዙ ሀገሮች ዘመን መለወጫ የነበረ ቢሆንም ሌሎቹ በተለያየ ሰው ሠራሽ ምክንያት ሌላ ቀመር በመፍጠር የነበረውን ትተው በሌላ እየተጠቀሙ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ ክብር ለእግዚአብሔር ይግባውና እኛ ኢትዮጵያውያን ብቻ በተሟላ ሁኔታ የጥንታውያን አበው ማለትም የአዳምና የኖኅ ሐሳበ ቀመር ይዘን መዝለቃችን ለእግዚአብሔርና ለቀደምት አበው ያለን ታማኝነት ምን ያህል ጠንካራ እንደሆነ ያሳያል፡፡ ይህ በራስ ሃይማኖት ትውፊትና ባህል ኮርቶ በልበ ሙሉነት የመኖር ጸጋችን የሀገርን ነፃነትና የሕዝብን አንድነት ለመጠበቅም ጒልህ ሚና እንደተጫወተ በደምብ መገንዘብ ያስፈልጋል ፡፡ የኢትዮጵያ ዘመን መለወጫ ርእሰ ዐውደ ዓመት ከሌሎች የዘመን መለወጫ በዓል ልዩ የሚያደርገው፤ በእግዚአብሔር የታዘዘ በአርእስተ አበው ዘመን የነበረ መሆኑ ብቻ አይደለም፤ ከነገረ ክርስቶስና ከሥነ ፍጥረትም በእጅጉ የተቈራኘ ምሥጢር አለው፡፡ ከነገረ ክርስቶስ አንጻር የክርሰቶስ መንገድ ጠራጊ የሆነው ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ የብሉይ ኪዳን ማብቂያና የሐዲስ ኪዳን መግቢያ መሆንና መስከረም አንድ ቀንም የአሮጌው ዓመት ማብቂያና የሐዲስ ዘመን መነሻ መሆን ተመሳሳይነት ስላላቸው የሁለቱን ንጽጽር በማገናኘት የዮሐንስ መታሰቢያ በዓል በርእሰ ዐውደ ዓመት እንዲከበር መደረጉ ነው፤ በተጨማሪም ይህ ንጽጽር ክርሰቶስ አሮጌውን ዓለም የሚያሳልፍ የሐዲስ ሰማይና የሐዲስ ምድር ጌታና ንጉሠ ነገሥት እንደሆነ የሚገልጽ ምሥጢር አለው፡፡ ከሥነ ፍጥረት አንጻር ሲታይ ደግሞ የክረምቱ የዝናም ውሽንፍር፣ የደመናው፣ የመብረቁ፣ የነጐድጓዱ፣ የጭፍናውና የጎርፉ ጋጋታ ሁሉ አልፎ ምድር በልምላሜና በአበባ ባሸበረቀችበት፣ ውኃው በየፏፏቴው በየሸለቈውና በየወንዙ ጥርት፣ ኮለል ብሎ በሚታይበት አዲስ እሸት በደረሰበት እንስሳቱም አእዋፉም በዝማሬና በደስታ በሚቦርቁበት ሰውም ከመልክዐ ምድር ውበት የተነሣ ልቡ በተስፋና በኃሤት በሚሞላበት የሚከበር የዘመን መለወጫ ርእሰ ዐውደ ዓመት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን፤

ይህ የዘመን መለወጫ በዓል በሁለመና ገጽታው ፍጹም መታደስን የሚያበስር ርእሰ ዐውደ ዓመት እንደሆነ በእግዚአብሔር ቃልም በሥነ ፍጥረትም ጭምር የተረጋገጠ መሆኑን በኅሊናችንም፣ በዐይናችንም የምናየው ሐቅ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ ሁሉ የሆነው ለማን ተብሎ እንደሆነ መገንዘብና መጠቀም ከፍጡራን ይጠበቃል፡፡ እግዚአብሔር የፍጥረታት መታደስን የሚወድ አምላክ እንደሆነ በሥነ – ፍጥረት ብቻ የገለጸ አምላክ አይደለም፤ በቅዱስ ቃሉም ‹‹በልባችሁ መታደስ ተለወጡ›› በማለት ሁሉም መታደስ እንዳለበት አስተምሮናል እንጂ፡፡ አዲስ የዘመን መለወጫ ብለን የምንናገርለት ይህ ዕለት አዲስ ሊሆን የሚችለው በዋናነት የኛ ልቡና ሲታደስ ነው፡፡ እግዚአብሔር ቃል ኪዳኑን ጠብቆ እነሆ ምድራችንን በልምላሜ፣ በአበባ፣ በፍሬ፣ በምርት በሁሉም ነገር አስውቦ አዲስ አድርጎአታል፡፡ እኛ ሰዎችም በተመሳሳይ በአስተሳሰብ በሥራ በአኗኗር ሁሉ ከልብ የሆነ መታደስ ሊኖረን ይገባል፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ ሕዳሴን እናበሥራለን›› የሚለው መልካም ምኞታችን ከቃላት አልፎ ተግባራዊ እንዲሆን ከሁሉም በፊት ይቅርታና እውነተኛ መግባባት በሁሉም ወገኖች መከናወን አለበት፤ አንድ መቀበል ያለብን እውነት በሐሳብ መቀራረብና በሰጥቶ መቀበል መርሕ እየተቻቻሉ መሄድ እንደ አዋጭ ባህል አድርገን መጓዝ ካልቻልን መቼም ቢሆን ለችግራችን መፍትሔ አናገኝም፤ ምክንያቱም በታሪክ የሁሉም ሐሳብ አንድ ዐይነት ሆኖ የተገኘበት ጊዜ የለምና ነው፡፡ ያለን ብቸኛ አማራጭ የተወሰነውን በመተው፣ የተወሰነውን በመቀበል፣ የተወሰነውን ደግሞ በመስጠት ወደ አንድነት መምጣትና ሀገርንና ወገንን ማሳደግ ነው፡፡ ይህ ዐይነቱ መቻቻል በሀገራችን ውስጥ ባለመዳበሩ ሕዝባችን ለመከራ ተጋልጦአል ፡፡

ይህ ዐይነቱ ክሥተት ከአሮጌው ዘመን ጋር አብሮ ማክተም አለበት፤ መለያየት፣ መገዳደል፣ ወገንን ማፈናቀል፣ አብያተ ሃይማኖትን መዳፈር፣ የእርጅና ምልክቶች ናቸውና ከአሮጌው ዓመት ጋር አብረው ማለፋቸውን በአዲሱ ዓመት እናብሥር፤ በምትኩም ለአንድነት፤ ለመፈቃቀር ለመተዛዘን፣ ለመቻቻል፣ ለመከባበር፣ ለመተማመንና ለአብሮነት መበልጸግ ከዛሬዋ ቀን ጀምረን በአዲስ ልብ በአዲስ መንፈስ መነሣት ይኖርብናል፡ ይህን ስናደርግ ዘመኑም፣ ሥነ ፍጥረቱም፣ እኛም በትክክል በሕዳሴ መንገድ መጓዝ ጀምረናል ማለት እንችላለን፡፡ የእግዚአብሔር በረከት በሕዝቦች አንድነት ውስጥ አለ፡፡ የነፃነትና የኀያልነት መንፈስ በሕዝቦች አንድነት ውስጥ አለ፡፡ ችግሮችን ሁሉ በብቃት ተቋቁሞ በአሸናፊነት መወጣት በሕዝቦች አንድነት ውስጥ አለ፡፡ አንድነት ከሌለ ጒልበት የለም፤ ችግሮችን መቋቋምም አይቻልም፤ በባዕዳን መደፈርም ሊከተል ይችላል፤ እግዚአብሐሔርም ፊቱን ያዞራል፡፡ ስለዚህ ይህ ታላቅና ባለታሪክ ሕዝብ ለዘመናት ተንከባክቦ ያቆየው ሃይማኖቱን፣ ታሪኩን፣ ባህሉንና አንድነቱን ይፈልጋልና አሁንም፣ ነገም፣ ከነገ በኋላም የሕዝቡን አንድነት እንጠብቅ፤ ለግል ፍላጎት ስንል በሕዝቡ አንድነትና እኩልነት መሰናክል አናብዛ፤ በምናደርገውም ሁሉ በእግዚአብሔርና በታሪክ ፊት በደል እንዳንፈጽም እንጠንቀቅ ፡፡

በመጨረሻም፡ አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የስምምነትና የይቅርታ ዘመን ማድረግ የምንችለው ከእግዚአብሔር በታች እኛው ነን፤ ስለሆነም በይቅርታና በሰጥቶ መቀበል መርሕ ሁሉንም ልዩነቶች ወደ መቀራረብ ብሎም ወደ ፍጹም መተማመን በማምጣት ሀገሪቱንና ሕዝቦችዋን ወደ አንድነትና ወደ ላቀ ሕዳሴ እንድናሸጋግር አደራ ጭምር መንፈሳዊና አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ፤ ይቀድስ ወስብሐት ለእግዘኢብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32019-09-12 13:54:072025-01-28 13:55:28መስከረም 1 ቀን 2012 ዓ.ም. የዘመን መለወጫ በዓልን ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጳጒሜን 2 ቀን 2011 ዓ.ም.የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ሊቀ አእላፍ በላይ መኮንን የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ለመክፈት ባዘጋጀው ቡድናዊ አሠራር መሠረት አሽቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ጠርቶ ለሦስት ቀናት ዝግ ጉባኤ አድርጎ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡ Link to: ጳጒሜን 2 ቀን 2011 ዓ.ም.የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ሊቀ አእላፍ በላይ መኮንን የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ለመክፈት ባዘጋጀው ቡድናዊ አሠራር መሠረት አሽቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ጠርቶ ለሦስት ቀናት ዝግ ጉባኤ አድርጎ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡ ጳጒሜን 2 ቀን 2011 ዓ.ም.የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ... Link to: መስከረም 16 ቀን 2012 ዓ.ም በመስቀል ደመራ በዓል ላይ የተላለፈ መልእክት Link to: መስከረም 16 ቀን 2012 ዓ.ም በመስቀል ደመራ በዓል ላይ የተላለፈ መልእክት መስከረም 16 ቀን 2012 ዓ.ም በመስቀል ደመራ በዓል ላይ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top