
የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች
የቤተ ክርስቲያናችን ዓላማ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ማስተማርና መንፈሳዊ አገልግሎትን ለእግዚአብሔርና ለሕዝበ ክርስቲያኑ ማበርከት ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ሳይዛባ፣ ሳይፋለስ፣ ፈሩን ሳይለቅ በነበረበት ለማስቀጠል የመንበረ ሐዋርያት ወራሾች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በዓመት ሁለት ጊዜ በቋሚነት እየተሰበሰቡ፣ ስለአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ እየገመገሙ፣ እየመከሩና እየወሰኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን እምነትዋንና ሥርዓቷን እንዲጠብቁ ቅዱሳን አበው በቀኖና ቤተ ክርስቲያን ደንግገዋል፡፡
በፌስቡክ ያግኙን


ጥቅምት 13 ቀን 2012 ዓ.ም. በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በልዩ ልዩ ምክንያቶች ሃይማኖትን፣ ብሔርና ቋንቋን መሠረት ያደረገ የሰው መግደልና የአብያተ ክርስቲያናት አስምልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በፍጹም የሚያወግዘው መሆኑን የተሰጠ መግለጫ በቅዱስነታቸው ተላልፏል፡፡
«ተገሐሥ እምእኩይ ወግበር ሠናየ -- ከክፉ ነገር ራቅ፤ ሰላምን ፈልጋት።»
(መዝ. 33፥12)

ጥቅምት 12 ቀን 2012 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
“ወይእዜኒ ረዐዩ ዘሀለዉ ኀቤክሙ መርዔቶ ለክርስቶስ፤ አሁንም በእናንተ ዘንድ ያሉትን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ (1ኛ ጴጥ. 2፥6)፡፡

ጳጒሜን 2 ቀን 2011 ዓ.ም.የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ሊቀ አእላፍ በላይ መኮንን የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ለመክፈት ባዘጋጀው ቡድናዊ አሠራር መሠረት አሽቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ጠርቶ ለሦስት ቀናት ዝግ ጉባኤ አድርጎ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡
ጳጒሜን 2 ቀን 2011 ዓ.ም.


ከግንቦት 14 ቀን እስከ ሰኔ 3 ቀን 2011 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡
የሕዝብና ቤት ቈጠራው በትክክል ይካሄድ፣ ስለተመለሡልን ሕንጻዎች በማመስገን ቤተ ክርስቲያናችን ከመንፈሳዊ አገልግሎት በተጨማሪ በማኅበራዊ ዘርፍ ለሀገር እድገትና ለሕዝቦች ኑሮ መሻሻል፣ በተለይም ለሀገራዊ ሰላምና አንድነት በመቆም ድርሻዋን እንድትወጣ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል