• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 24 ቀን 2012 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡

November 4, 2019

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቍጥር 164 ድንጋጌ መሠረት ከጥቅምት 12 እስከ ጥቅምት 24 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ የተካሄደውን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አስመልከቶ የተሰጠ መግለጫ፤
1. ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የመክፈቻ ንግግር ሆኖ ለምልአተ ጉባኤው የቀረበው መልእክት በቀጣይ በቤተ ክርስቲያናችን ለሚከናወነው መንፈሳዊውም ሆነ ማህበራዊ ተልእኮ ጠቃሚነቱ የጐላ በመሆኑ ጉባኤው የሥራ መመሪያ አድርጎ ተቀብሎታል፡፡
2. የሀገር ሰላምን ጉዳይ አስመልክቶ በአሁኑ ጊዜ በአገራችን ኢትዮጵያ እየታየ ያለው የሰው ሕይወት መጥፋትና የዜጎች ንብረት መውደም፣ ቅዱስ ሲኖዶሱን በእጅጉ ያሳዘነ ሲሆን፣ መንግሥት ለጉዳዩ ትኵረት ሰጥቶ ሰላምን እንዲያስከብር፣ የዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ እንዲያደርግ፣ የተፈናቀሉትም ወደቀያቸው እንዲመለሱና ለጠፋው ንብረታቸው ማቋቋሚያ እንዲደረግላቸው፣ በተለይም በክርስቲያኖችና በአብያተ ክርስቲያናት ላይ እየደረሰ ያለው ስደትና መከራ ጐልቶ እየታየ በመሆኑ የጥፋቱ መልእክተኞችን መንግሥት በሕግ እንዲጠየቁ እንዲያደርግ ቅዱስ ሲኖዶስ እያሳሰበ መንግሥትም ለሕዝቡ ብርቱ የበኩሉን ጥበቃ እንዲያደርግ፣
3. በቤተ ክርስቲያናችን የሚከናወነውን መንፈሳዊም ይሁን ማኅበራዊ ተግባራት በአግባቡ ማስተላለፍ እንዲቻል የቤተ ክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት በመምሪያ ደረጃ እንዲቋቋም፣
4. በአገራችን በተለያዩ ክልሎች የተለያዩ ቋንቋ ተናጋሪዎች በብዛት እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የቤተ ክርስቲያኒቱን ተከታዮች በቋንቋቸው ማስተማርና ማገልገል እንዲቻል በየአህጉረ ስብከቶቹ የሚገኙ የአብነት ት/ቤቶችን ማጠናከር ከልዩ ልዩ ቋንቋ ተናጋሪዎች አገልጋዮችን ማፍራት እንዲቻል ለት/ቤቶቹ ማጠናከሪያ የሚሆን ቋሚ በጀት እንዲመደብ፣ በቀጣይም በሁሉም አፍ መፍቻ ቋንቋ በማእከል ማሠልጠኛ እንዲቋቋም፤
5. የአገራችን ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በሀገራችንና በአፍሪካ ጭምር ያበረከቱት የሰላም ተልእኮ አስመልክቶ ዓለም ዐቀፍ የኖቤል ተሸላሚ መሆናቸው፣ በተለይም ለአገራችን ኢትዮጵያ ከፍተኛ ዕውቅና ያስገኘላት ቀድሞም የነበረ ክብሯን አጒልቶ ያሳየ በመሆኑ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አድናቆቱን ገልጿል፡፡ ለወደፊቱም ለአገራችን እድገትና ብልጽግና በመንግሥት በኩል ለሚሠራው ማኅበራዊና ልማታዊ ሥራ ቤተ ክርስቲያናችን አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ትቀጥላለች፡፡
6. አገራችን ኢትዮጵያ በጀመረችው የልማት አቅጣጫ በስፋት ለማስቀጠልና በተለይም ዜጎችን ከድህነት ለማላቀቅ በእጅጉ ተስፋ የተጣለበት የዐባይ ግድብ በተያዘው የግንባታ ሥራ ተፋጥኖ ግድቡ እንዲጠናቀቅና ሥራ እንዲጀምር ለማስቻል መላው የአገራችን ሕዝቦች አስፈላጊውን እገዛ በማድረግ እንዲቀጥሉ ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፡፡
7. የቤተ ክርስቲያናችንን አጠቃላይ መሪ ዕቅድ በተመለከተ ቀደም ሲል በቅዱስ ሲኖዶስ በተወሰነው መሠረት በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ በኩል ወደተግባር እየተገባ መሆኑን ጉባኤው ከቀረበው ሪፖርት አዳምጧል፡፡ በቀጣይም ሥራው ተፋጥኖ እንዲቀጥልና ከካህናት ከምእመናን ከወጣቱም ጭምር የሚቀርቡ ወቅታዊ አቤቱታዎች በመሪ ዕቅዱ እየተጠኑ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ ተወስኗል፡፡
8. በግንቦቱ ርክበ ካህናት በቤተ ክርስቲያናችን የተቋቋመው አገራዊ የሰላምና የዕርቅ ኮሚቴ የ4 ወራት ሪፖርት ለጉባኤው አቅርቧል፡፡ ኮሚቴውም ያከናወነው የሰላም ተልእኮ ጉባኤው በአድናቆት ተቀብሎ በቀጣይም ኮሚቴው ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከምሁራንና ከወጣቶች የተውጣጡ አባላትን አካቶ የሰላምና የዕርቅ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል በማሳሰብ፣ ለዚህም የሚሆን አስፈላጊ በጀት መድቧል፡፡
9. በአገራችን በኢትዮጵያ በኦሮምያ ክልል በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ በደረሰው የሰው ሕይወት መጥፋትና ስደት ላይ በመነጋገር በጣም ለተቸገሩ ወገኖች በጊዜያዊነት የሚደርስ ምግብና አልባሳት ለማቅረብ እንዲቻል አስፈላጊውን ገንዘብ እንዲመደብ፣ በቀጣይም በክልሉ ይህንን ችግር እየተከታተለ ዘለቄታዊ ርዳታ የሚያሰባስብ ኮሚቴ እንዲቋቋም ተወስኗል፡፡
10. የጌዴኦና ቡርጂ ዞኖች እስከ አሁን ድረስ በሲዳማ ሀገረ ስብከት ሥር ሆነው መንፈሳዊውን አገልግሎት ሲያገኙና ሲተዳደሩ የቆየ ቢሆንም በአሁኑ ጊዜ ራሱን ችሎ ሀገረ ስብከት እንዲሆንላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት ራሱን የቻለ ሀገረ ስብከት እንዲሆን ተወስኗል፡፡
11. በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና በሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሞስኮ መንበረ ፓትርያርክ መካከል ሊኖር ስለሚገባው ግንኙነት በተመለከተ ከቤተ ክርስቲያናችን የውጭ ግኑኝነት መምሪያ በቀረበ ሪፖርት ላይ ጉባኤው ተነጋግሮ በሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት የነበረው ጥንታዊ ግንኙነት ወደፊትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡
12. በስዊድን ሀገር ሶደርቴሌ ከተማን ማእከል ያደረገ የቅዱስ አግናጥዮስ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ሴሚናሪ በመላው አውሮፓ ለሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን እና አገልጋይ ካህናት ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ጥንታዊ የአብነት ትምህርትና ዘመናዊ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ነገረ መለኮት ሥልጠና የሚሰጥ ከፍተኛ የትምህርት ማእከል በመሆኑ በቤተ ክርስቲያናችን ስም ዕውቅና እንዲያኝ ተወስኗል፡፡ አገልግሎቱን በስፋትና በብቃት እንዲያከናውን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም የዕውቅና ደብዳቤ እንዲደርሰውም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ወስኗል፡፡
13. የ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ በጀት አስመልክቶ ከበጀትና ሂሣብ መምሪያ በቀረበው ዕቅድ ላይ በመነጋገር የቀረበው በጀት ላይ ማሻሻያ በማድረግ የ2012 ዓ.ም. በጀት በማጽደቅ በሥራ ላይ እንዲውል ተወስኗል፡፡
14. በአሁኑ ጊዜ በአገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እየታየ ያለው ችግር እንዲያበቃ እግዚአብሔር አምላክ ምሕረቱን እንዲሰጠን የተጀመረው ሱባኤ እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡

ጥንታዊትና ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ከጥንት ጀምሮ የአገር ባለውለታ እንደመሆኗ ሁሉ ወደፊትም በአገራችን ኢትዮጵያ በመንግሥትና በሕዝቡ ትብብር ለአገር አንድነትና ለዜጎች መብት መከበር፣ ለሰው ልጆች እኩልነት ለሚደረገው አገራዊ ጥረት የበኩሏን አስተዋፅኦ ከማድረግ አትቈጠብም፡፡ ሆኖም ለዚሁ አገራዊ ስኬት ከሁሉም በላይ በዜጎች መካከል መከባበርና ሰላማዊ አንድነት መኖር ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ያምናል፡፡ ስለዚህ ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ሁሉ በአሁኑ ጊዜ ለአገራዊ አንድነታችን ሰላም ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን አምናችሁ በአንድነት በሰላምና ተከባብሮ በጋራ ለመኖር፣ ለመሥራትም ሆነ ሠርቶ ለመበልጸግ አገራዊ አንድነታችሁን እንድታጠናክሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

የአገራችን መንግሥትም የአገር ሰላም፣ የዜጎች ደኅንነትና በሰላም ወጥቶ መግባት ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑን፣ ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ሕይወት በምንም መልኩ በከንቱ መጥፋት የሌለበት መሆኑን ተገንዝቦ፣ ሰላምን የማስከበሩን፣ አገር የመጠበቁንና ዜጎችን በአገራቸው በእኩልነት ተሳስበው የሚኖሩበትን መንገድ በመቀየስ መንግሥታዊ ኀላፊነቱን እንዲወጣ ቅዱስ ሲኖዶስ አጥብቆ ያሳስባል፡፡

በመጨረሻም ከጥቅምት 11 እስከ 24 ቀን ለ13 ቀናት በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊና ማኅበራዊ እንዲሁም አገራዊ ጉዳዮች ላይ ሲነጋገር የቆየው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በሰላም ተጠናቅቆ በዛሬው ቀን በጸሎት ተዘግቷል፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32019-11-04 09:46:182025-01-27 09:47:56ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 24 ቀን 2012 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጥቅምት 13 ቀን 2012 ዓ.ም. በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በልዩ ልዩ ምክንያቶች ሃይማኖትን፣ ብሔርና ቋንቋን መሠረት ያደረገ የሰው መግደልና የአብያተ ክርስቲያናት አስምልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በፍጹም የሚያወግዘው መሆኑን የተሰጠ መግለጫ በቅዱስነታቸው ተላልፏል፡፡ Link to: ጥቅምት 13 ቀን 2012 ዓ.ም. በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በልዩ ልዩ ምክንያቶች ሃይማኖትን፣ ብሔርና ቋንቋን መሠረት ያደረገ የሰው መግደልና የአብያተ ክርስቲያናት አስምልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በፍጹም የሚያወግዘው መሆኑን የተሰጠ መግለጫ በቅዱስነታቸው ተላልፏል፡፡ ጥቅምት 13 ቀን 2012 ዓ.ም. በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች... Link to: ታኅሣሥ 28 ቀን 2012 ዓ.ም፡ የበዓለ ልደት ቃለ በረከት አስተላልፈዋል Link to: ታኅሣሥ 28 ቀን 2012 ዓ.ም፡ የበዓለ ልደት ቃለ በረከት አስተላልፈዋል ታኅሣሥ 28 ቀን 2012 ዓ.ም፡ የበዓለ ልደት ቃለ በረከት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top