• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ታኅሣሥ 28 ቀን 2012 ዓ.ም፡ የበዓለ ልደት ቃለ በረከት አስተላልፈዋል

January 7, 2020

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤ በሕመም ምክንያት በየጸበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ በልደቱ “ሰላም በምድር ይሁን” የሚል የሰላም መዝሙርን ያሰማን ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሁለተኛው ዓመት በዓለ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ !!

‹‹ተወልደ እምአመቱ ወሰላመ ገብረ በልደቱ፤
ከአገልጋዩ ተወለደ፤ በልደቱም ሰላምን አደረገ።››
(ቅዱስ ያሬድ)

በዓለ ልደተ ክርስቶስን ባነሣን ቊጥር በኅሊናችን ፈጥኖ የሚታወሰን ትልቅ ትዝታ፣ መላእክትና እረኞች በቤተልሔም ተገኝተው ‹‹‹ ሰላም በምድር ይሁን›› በማለት በአንድነት የዘመሩትን መዝሙር ነው፤በእርግጥም ይህ መዝሙር ጌታችን ሰው ሆኖ ከቅድስት ድንግል ማርያም በመወለድ በዚህ ዓለም የተገለጠበትን ምሥጢር የሚተረጕም ነው፡፡ ሁሉም እንደሚገነዘበው የሰላም ዋጋና ጣዕም በሰማይም ሆነ በምድር መተኪያ የማይገኝለት ነው፤በሰውና በእግዚአብሔር፣ በሰውና በመላእክት እንደዚሁም በሰውና በሰው መካከል ተገድግዶ የነበረው የጥል ግድግዳ ለሰው ብቻ ሳይሆን ለመላእክት ተልእኮም ዕንቅፋት መሆኑ አልቀረም፤ ምክንያቱም መላእክት በአርኣያ እግዚአብሔር የተፈጠረው ሰው ከቅድስና ስፍራ ተባርሮ በጐስቋላ ሕይወት ኑሮውን ሲገፋ ባዩ ቊጥር ደስታቸው ፍጹም አልነበረምና ነው፡፡ የቅዱሳን መላእክት ደስታ ፍጹም የሚሆነው ሰዎች በተመደበላቸው የክብር ስፍራ ሲገኙ እንደሆነ “በአንድ ሰው ንስሓ መግባት በሰማይ ታላቅ ደስታ ይሆናል” ተብሎ የተነገረው አምላካዊ ቃል በቂ ማስረጃ ነው፡፡ በልደተ ክርስቶስ ቀን ግን ከዚህም አልፎ በጐስቋላ ይሕወት ይማቅቅ የነበረው ሰው በተዋሕዶተ መለኮት በመንበረ ጸባኦት ዙፋን ተቀምጦ አይተዋል፤ከዚህም በመነሣት እግዚአብሔር ሰውን ከመታረቁና ከመሙደዱም በላይ በተዋሕዶ የሰው አካልና ባሕርይን የራሱ አካልና ባሕርይ ማድረጉን አስተውለዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር የሆነው ድርጊት በትክክል ሊገልጥ በሚችል አገላለጽ ‹‹እግዚአብሔር ሰውን በእጅጉ ወደደው በሰላምም ጐበኘው፤ ይህንንም ስላደረገ ከፍ ያለ ምስጋና ለእግዚአብሔር ይገባል›› በማለት መላእክትና ሰዎች የዘመሩት፣ መዝሙር በደማቅ ብርሃን የታጀበ ሰማያውያን ሠራዊትና ሰዎች በአንድነት የተሳተፉበት ድንቅ የሆነ የሰላም መዝሙር ነበር፡፡

ሰላም ለምድራውያን ብቻ ሳይሆን ለሰማያውያንም ውድና በጣም ተፈላጊ ስለ መሆኗ በልደተ ክርስቶስ ዕለት የተፈጸመው ሁናቴ ትልቅ መምህራችን ነው፤ያለ ሰላም ሃይማኖታዊ ሥርዐትን በአግባቡ ማካሄድ አይቻልም፤ ትምህርተ ሃይማኖትን አስተምሮ ማሳመንም አይቻልም፤ ሰላም ሳይኖር በልቶ፣ ጠጥቶና አጊጦ መኖር አይቻልም፤ ሰላም ሳይኖር ተምሮ መመረቅ፣ነግዶ ማትረፍ፣ አርሶ ማምረት፣ወልዶ ማሳደግ፣ድሮ መኳል የለም፤ሰላም ከደፈረሰ የኅብረተሰብ ኑሮ ይናጋል፤ ልማት ይቆማል፣ ድህነትና ችግር ይንሰራፋል፤ በመሆኑም የሰላም ጥያቄ የህልውና ቊጥር አንድ ጥያቄ መሆኑን ተገንዝበን ትልቁም ትንሹም፣ ሕዝብም መንግሥትም ከምንም በላይ ለሰላም ያለመታከት መሥራት አለብን፡፡ በዛሬው ዕለት የምናከብረው በዓለ ልደተ ክርስቶስም ለሰላም ተብሎ የሚከበር በዓል መሆኑን ማጤን ተገቢ ነው፤ይህ በዓል አካላዊ ቃል የሆነው እግዚአብሔር ወልድ አካላችንን አካል እስከ ማድረግ ደርሶ ምሕረትንና ይቅርታን ለሁላችን ማድረጉን በማስተማር የሚከበር በዓል ነው፡፡ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በልደቱ ሰላምን የሰበከልን፣ለሰው ልጆች በዚህም ሆነ በወዲያኛው ዓለም ከሰላም የበለጠ አስፈላጊ ነገር እንደሌለ ስለሚያውቅ ነው፤ሰላም ካለ ሌላው ሁሉ በሰላም ውስጥ ይገኛልና፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን፡ ዛሬ በዓለም ዙሪያ ሁሉ የሚስተዋለው የጦርነት ሥጋት፣ የበሽታዎች መዛመት፣ የስደተኞች ንረት፣ የፍትሕና የእኩልነት መዛባት ምንጫቸው የሰላም ዕጦት እንደሆነ አንስተውም፤ የሰው ኅሊና በሰላም አየር የተሞላ ቢሆን ኖሮ ሥጋቱ ይቀርና ለአጥፊ መሣሪያና ለመሳሰለው የሚወጣው ወጪ ለልማትና ለድሆች ድጋፍ ይውል ነበር፣ የዓለማችንን ችግር ለማስወገድ ለጦርነት የሚወጣው ወጭ ከበቂም በላይ እንደሆነ ጥርጥር የለውም፡፡ እግዚአብሔር በሀብተ ጸጋ የተሞላች ምድር ቢሰጠንም በራሳችን ደካማ አያያዝና የተሳሳተ አመለካከት ወደ ድህነት እየቀየርናት ነው፤ለሰው ልጆች ሰላምና ደግነት መጠበቂያ የሆነው ትምህርተ ሃይማኖትም ለነገር ትንኮሳና ለጠብ መጫሪያነት መጠቀም የተለመደ ሆኖአል፤ ነገር ግን የሃይማኖት ትንኮሳ ሌላውን ሳይሆን ተመልሶ ራስን ለባሰ አደጋ የሚያጋልጥ መሆኑን ሃይማኖታውያን ሁሉ በውል መገንዘብ ይኖርብናል፡፡

በተለይም ወጣት ልጆቻችን፣ እርስ በርስ ተፋቀሩ እንጂ ተጣሉ የሚል ሃይማኖት የሌለ መሆኑን፣ ነፍስን አድኑ እንጂ ግደሉ የሚል ሃይማትም እንደሌለ በትክክል ልታውቁ ይገባል፤ የሃይማኖት አስተምህሮ ምን ጊዜም ሰላምና ፍቅር ብቻ ነው፤ይህንን በቅጡ ያልተገነዘቡ ወገኖች ስሕተት ቢፈጽሙ እንኳ ስሕተትን በስሕተት ማረም ፍጽሞ አይቻልም፤ ስሕተት በሕግና በትምህርት ብቻ እንዲታረም ማድረግ እንጂ በስሕተት ላይ ስሕተት፣ በጥፋት ላይ ጥፋት በማከል ችግርን ማስፋፋት መፍትሔ አያመጣም ፡፡ የጐበጠውን ለማቅናት እንጂ የበለጠ እንዲጎብጥ ለማድረግ እግዚአብሔር እኛን አልጠራንምና በተጠራንበት ጥሪ ጸንቶ መኖር ከኛ ይጠበቃል፡፡ እኛ ክርስቲያኖች በዓለ ልደትን ስናከብር ሀገራዊ አንድነታችንንና ሁለንተናዊ ሰላማችንን ለማረጋገጥ ቃል መግባት ከሁላችን ይጠበቃል፡፡ ከዚሁም ጋር በልዩ ልዩ ምክንያት ችግር አጋጥሞአቸው የሚበሉትንና የሚጠጡትን፣ የሚለብሱትንና የሚጠለሉበትን ያጡ ወገኖችቻን ካለን በማካፈል በዓሉን ከኛ ጋር በደስታ እንዲያሳልፉ ማድረግ ይገባናል፡፡ ሕዝበ ክርስቲያኑ በዚህ ሁሉ ሃይማኖታዊ ግዴታውን እንዲወጣ አባታዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

በመጨረሻም፤ ያለ ሰላምና መረጋጋት መምረጥም ሆነ መመረጥ፣ መምራትም ሆነ መመራት እንደሌለ ሁላችንም እናውቃለን፤ በመሆኑም ሁሉም የፖለቲካ ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የሚድያ ባለሙያዎች የሀገርን ሰላምና አንድነትን ተቀዳሚ አጀንዳ አድርጋችሁ ኀላፊነት ባልተለየው ጥበብ ሥራችሁን እንድታከናውኑ፣ ሕዝቡም በተለይም ወጣቱ ትውልድ ሰላምን ከሚያደፈርሱ ተግባራት ተቈጥቦ፣ በምትኩ ሠርቶ የሚያተርፍበትን አማራጭ በማፈላለግ ለሀገር ልማት እንዲነሣሣ አደራ ጭምር አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

መልካም በዓለ ልደት ያድርግልን እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ‹‹ወስብሐት ለእግዚአብሔር››

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32020-01-07 13:57:442025-01-28 13:58:38ታኅሣሥ 28 ቀን 2012 ዓ.ም፡ የበዓለ ልደት ቃለ በረከት አስተላልፈዋል
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 24 ቀን 2012 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ Link to: ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 24 ቀን 2012 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 24 ቀን 2012 ዓ.ም የተካሄደው... Link to: ጥር 11 ቀን 2012 ዓ.ም የጥምቀት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥር 11 ቀን 2012 ዓ.ም የጥምቀት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥር 11 ቀን 2012 ዓ.ም የጥምቀት በዓል ቃለ ምዕዳንና...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top