• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

መስከረም 16 ቀን 2014 ዓ.ም. የመስቀል ደመራ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

September 26, 2021

በስመ አብ፣ወወልድ፣ወመንፈስ ቅዱስ፣አሐዱ አምላክ፤

“መስቀል መልዕልተ ኲሉ ነገር
መስቀል ከሁሉም ነገር በላይ ነው፤”
(ቅዱስ ያሬድ)

ስለ ቅዱስ መስቀል ምሥጢራዊ ትርጒም በምናስተውልበት ጊዜ በውስጡ ሰፊና ጥልቅ የሆነ ምሥጢረ መለኮት ይዞ እናገኘዋለን። ይሁንና በአጭር አገላለጽ ስናስቀምጠው መስቀል ከመርገም ተነሥቶ፣በመሥዋዕትነት ተራምዶ፣ ሰላምንና ዕርቅን ያስገኘ፣ የመጨረሻ ተግባሩንም ሰውን በማዳን ያጠናቀቀ የነገረ ድነት ጠቅላይ ነገር ነው። ቅዱስ ያሬድ መስቀል ከሁሉም ነገር በላይ ነው ሲል የተናገረው ከዚህ የተነሣ ነው፡፡ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውን ከኀጢአትና ከሞት ለማዳን በተገለጠ ጊዜ፣ከዕለተ ፅንሰቱ አንሥቶ እስከ ዕለተ ስቅለቱ ያከናወነው ግብረ አድኖ ሁሉ የነገረ መስቀሉ አካል ነው&በሌላ አባባል የጌታችን ተግባር ሁሉ የማዳን ተግባር ነው ማለት ነው። መዳን ሲነሣ ከሱ በፊት ጕዳት እንዳለ መገንዘብ አያዳግትም&በመሆኑም በግብረ ኀጢአት የወደቀው የሰው ልጅ ከበደሉ የተነሣ እሱና የሚኖርባት ምድር በጽኑ መረገማቸው ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል። ጉዳቱ ይህ ነበር፤ ክርስቶስ አምላካችንም በዚህ ዓለም የተገለጸው የዚህ መርገም ተሸካሚ በሆንነው በእኛ ፈንታ መርገማችንን ተሸክሞ በመስቀል ላይ በመሰቀል ሊያድነን ነው። ከቅዱስ መጽሐፍ አስተምህሮ እንደምንረዳው ከዘመነ ክርስቶስ በፊት “በመስቀል ተሰቅሎ የሚሞት ሁሉ የተረገመ ነው” ተብሎ ተጽፎል፤ ከዚህ አንጻር በመስቀል ላይ መሰቀል የነበረበት ያው መርገመ ኀጢአት ያለበት የሰው ልጅ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡

ይሁን እንጂ እግዚአብሔር በማይነገር ምሕረቱና ፍቅሩ ሰውን ከፍዳ መርገም ሊታደገው ሲፈልግ፣ መርገም ሳይኖርበት በርግማን ፈንታ ቤዛ ሆኖ በመስቀል ላይ በመሰቀል ሰውን እንዲያድን አንድ ልጁን ወደ እኛ ላከ፤ እሱም ይህንን በመስቀል ላይ በተግባር ፈጸመ፤ በዚህም ምክንያት የመርገመ አዳም ፋይል ስለተዘጋ በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ዕርቅ ወረደ& ሰላምም ሰፈነ&ሰውም ከፍዳ መርገም ዳነ፤ ምክንያቱም ድነት ወይም ደንነት የዕርቅና የሰላም ውጤት ነውና፤ ቅዱስ መጽሐፍ ይህንን በተመለከተ“ወገብረ ሰላመ በደመ መስቀሉ ለዘበሰማይ ወለዘበምድር፤ &በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙ በሰማይና በምድር ላሉት ሰላምን አደረገ” ሲል ያበሥራል፤ በዚህም ክርስቶሳዊ ቤዛነት ሰው ፍጹም ይቅርታና ምሕረት አግኝቶ ወደ አባቱ ወደ እግዚአብሔር ሊቀርብ ቻለ፤ ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው ሱታፌም እንደገና ሊቀጥል በቃ፤ በመሆኑም በዚህ አምላካዊ ምስጢር ሰው ወደ ቀደመ ቦታው ወደ ገነት ገባ&ይህ እጅግ ታላቅና አስገራሚ ፍቅር የተገኘው በመስቀል በመሰቀል ነውና መስቀል ከሁሉም ነገር በላይ ነው ሊባል ችሏል፡፡ የመስቀል ዕርቀ ሰላምና አድኖ በዕለተ ስቅለቱ ብቻ ተሠርቶ ያለቀና የተጠናቀቀ አይደለም፤ በዚያ የተጠናቀቀው የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ነገረ አድኖ ነው&የእኛ ሰላምና ዕርቅ ግን ዕለት ዕለት በየጊዜው ያለማቋረጥ ልንፈጽመው የሚገባ የቤት ሥራ ነው&በልብሳችን ያሳተምነው&በአካላችን ያስነቀስነው ትእምርተ መስቀል ለጌጥ ወይም ለመመጻደቅ ከሆነ ተሳስተናል፤ ይልቁንም የመስቀል ትርጒም ሰላምና ዕርቅ ስለሆነ በእግዚአብሔርና በእኛ መካከል&በእኛና በእኛ መካከል፣ በእኛና በሥነ ፍጥረት መካከል ያለውን ሰላምና ዕርቅ ልንጠብቅበት ይገባል፤ በምድራችንም ሆነ በዓለማችን ፍጹም ሰላም አለ ብለን ደፍረን መናገር የምንችለው እኛ ከእግዚአብሔር፣ ከሰውና ከሥነ ፍጥረት ጋር ሰላምና ዕርቅ ሲኖረን ነው& መዳን የምንችለውም ይህንን ስንከተል ነው፤ በልብሳችንና በአካላችን አንቈጥቊጠን የምናሳየው ትእምርተ መስቀል ሰላምና ዕርቅ እስከ ውስጣዊው አካላችን ሠርፆ እንዲገባ ሊያሳስበን፤ ሊያስታውሰንና ሊቀሰቅሰን እንጂ ለሌላ አይደለም፤ ስለሆነም የሰው ልጅ ሁሉ በተለይም ሕዝበ ክርስቲያኑ በዚህ ዓለም የሰላምና ዕርቅ አምባሳደር ሆኖ እንዲሠራ በእግዚአብሔር የተሾመ መሆኑን ሊያስተውል ይገባል፡፡

በዛሬው ዕለት የምናከብረው በዓለ መስቀል የእግዚአብሔርን ሰላምና ዕርቅ ፈልጋ በብርቱ የተንቀሳቀሳችው ታላቋ ክርስቲያናዊት ንግሥት ዕሌኒ የፈጸመችውን የቅድስና ተግባርና ያስገኘችውን ሃይማኖታዊ ስኬት መነሻ አድርገን ከእግዚአብሔር ጋር ለመታረቅ ነው፤ በዚህ አጋጣሚ በዛሬው ዕለት ለመላው የዓለም ማበረሰብም ሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የምናስተላልፈው መልእክት “እባካችሁ የመስቀሉን ሰላምና ዕርቅ እናክብር” የሚለውን ነው፡፡ ስለ ሰላምና ዕርቅ ሲነገረን ጆሮአችንን አንድፈን፣ ዐይናችንን አንጨፍን፣ ፊታችንን አናዙር፣ በራችንን አንዝጋ፣ሰላምና ዕርቅ እኮ ፍቱን የሆነ የሕይወትና የንብረት የዋስትና መድኀኒት ነው፤ ሰላምና ዕርቅ የእድገት፣ የጤና እና የልማት ጒዞ ነው፤ ሰላምና ዕርቅ እኮ አሸናፊነትን እንጂ ተሸናፊነትን አያስከትልም፣ ሰላምና ዕርቅ እኮ ወደ እግዚአብሔር በሞገስና በክብር የሚያቀርብ መለኮታዊ ፈውስ ነው፤ ከዚህ አኳያ ስለ ሰላምና ዕርቅ አስመልክቶ የሚሰማው ድምፅ ከሰው የመጣ ድምፅ ሳይሆን ከእግዚአብሔር የመጣ ድምፅ መሆኑን አውቀን መልሳችን አዎንታዊ ሊሆን ይገባል፤ ሌላው ሁሉ ከዚያ በኋላ ይሆናል፡፡

እንደ እውነቱ ከሆነ በድርድር፣በውይይት፣በሰጥቶ መቀበልና በይቅርታ የማይፈታ ችግር ከቶ የለም፤ እነዚህን እንዳናደርግ ማን ከለከለን? ከነዚህስ በቀር የሚጠቅመን ሌላ ምን ነገር አለ? የችግር ሁሉ መቋጯስ ውይይት ካልሆነ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?ታድያ ይህ የተሻለ አማራጭ እያለ ለምን ሕይወት ይጠፋል? ለምንስ ንብረት ይወድማል? ወንድምስ በወንድሙ ላይ ለምን ይጨክናል? አሁንስ ሄዶ ሄዶ ወደ ውይይት መግባቱ መቼ ይቀራል; ነገር ግን ከዚህ ሳይደረስ ቢደረግ መልካም ነበረ፤ ለሰላምና ዕርቅ ዋጋ ሳንሰጥ የመስቀሉን በዓል ማክበር ብቻ ትርጒም ይኖረዋል ብለን የምናስብ ከሆነ የመስቀሉን ምሥጢር በቅጡ አልተረዳነውም ማለት ነው፣እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ አብልጦ የሚመለከተው እኛን እንጂ የመስቀሉን በዓል አይደለም፤ እኛ እየተጣላን በዓለ መስቀሉን ብናከብር፣ እግዚአብሔር የማይቀበለው መሥዋዕት እንደሆነ እንወቅ፡፡ ከዚህ አንጻር ታላላቅ የሃይማኖት መሪዎችና ሊቃውንት፣ አሉ የተባሉ የሀገር ሽማግሌዎች፣ እጅግ የተራቀቁ ምሁራን እንደዚሁም የበሰሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚገኙባት በታላቋ ሀገር በኢትዮጵያ የተከሠተው ክሥተት ለሕዝባችን የሚመጥን አይደለም፤ ከሃይማኖታችንና ከታሪካችን ጋርም አብሮ የሚሄድ አይደለም፤ ይህ በብርቱ ሊታሰብበት ይገባል፤ ከእንግዲህ ወዲህ የእስካሁኑ በቅቶን ሌላውም ሁሉ ለጊዜው አቆይተን፣እንደ መስቀል መርሕ በሰላምና ዕርቅ ጥበብ የሕይወት አድን ሥራን በቁርጥ እንድንሠራ ማለትም በማናቸውም ምክንያት የሰው ሕይወት እንዳይጠፋ ጠንካራ ሥራ እንድንሠራ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡

መልካም በዓለ መስቀል።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ይቀድስ፤
ወስብሐት ለእግዚአብሔር።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32021-09-26 14:16:382025-01-28 14:17:25መስከረም 16 ቀን 2014 ዓ.ም. የመስቀል ደመራ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: መስከረም 1 ቀን 2014 ዓ.ም ቅዱስነታቸው ዘመን መለወጫ በዓል አስመልከቶ የሰጡት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: መስከረም 1 ቀን 2014 ዓ.ም ቅዱስነታቸው ዘመን መለወጫ በዓል አስመልከቶ የሰጡት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ መስከረም 1 ቀን 2014 ዓ.ም ቅዱስነታቸው ዘመን መለወጫ... Link to: ጥቅምት 8 ቀን 2014 ዓ.ም 40ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ Link to: ጥቅምት 8 ቀን 2014 ዓ.ም 40ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ ጥቅምት 8 ቀን 2014 ዓ.ም 40ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top