• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

የካቲት 11 ቀን 2012 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የእነ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን ሥልጣነ ክህነት በውሳኔ ማገዱን ቅዱስነታቸው እንደሚከተለው ገልጸዋል፡፡

February 19, 2020

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቤተ ክርስቲያኒቱና በምእመናን ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር አስመልክቶ ከየካቲት 9 -11 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ተነጋግሮ በቤተ ክርስቲያናችን በተለያዩ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም የቤተ ክርስቲያናችን ተከታይ የሆኑ ምእመናን ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር አስመልክቶ በመነጋገር እና ውሳኔ በማሳለፍ የሚከተለውን መግለጫ አውጥቷል፡፡

1. በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 እና 5 በቀድሞው ቀበሌ 24/18/16 እና 15 ነዋሪዎች ለቅዱስ ሲኖዶስ ባቀረቡት አቤቱታ እንደተገለጸው በ24/5/2012 ዓ.ም. ለ25 አጥቢያ በውድቅት ሌሊት በቦሌ ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን በርካታ የሆኑ ምእመናን በምሕላና በጸሎት ላይ እያሉ በተኵስና አስለቃሽ የመርዝ ጋዝ ጭስ በመጠቀም በጥይትና በዱላ በርካታ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱ ሁለት የቤተ ክርስቲያናችን አማንያን ወጣቶች መገደላቸውን ቤተ ክርስቲያኑ ፈርሶ ክቡር የሆነውና በአባቶች ተባርኮ የነበረው የቃል ኪዳን ጽላት መወሰዱ፣ የቤተ ክርስቲያኑ ንዋያተ ቅድሳት መዘረፋቸውን የሰማው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በድርጊቱ እጅግ ከማዘኑም በላይ ይህን ክፉና ጭካኔ የተመላበት ድርጊት አውግዟል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችንም ላይ እንዲህ ዐይነት ክፉ ድርጊት የፈጸሙ አካላት ላይ መንግሥት ጥብቅ ምርመራ በማድረግ ወንጀለኞቹ ለፍርድ እንዲቀርቡና ውጤቱ ለምእመናኖቻችን በሚዲያ እንዲገለጽ እንጠይቃለን፡፡
2. የቤተ ክርስቲያኒቱን ቦታ በተመለከተ ቤተ ክርስቲያናችን ከአራት ዓመታት በፊት ጀምሮ ቦታው ለአካባቢው ምእመናን ማምለኪያ እንዲሆን ከመንግሥት በመነጋገርና በመጻጻፍ የቆየችበት ከታቦተ ሕጉ ጀምሮ ንዋያተ ቅድሳት የከበሩበት ከመሆኑም ባሻገር ሁለቱ የቤተ ክርስቲያናችን አማንያን ወጣቶች በግፍ ጨለማን ተገን ባደረጉ የመንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎች ደማቸው የፈሰሰበትና ሕይወታቸው ያለፈበት ቅዱስ ቦታ እንደመሆኑ መጠን ወደ ቀደመ ክብሩ ተመልሶ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ ምእመናን በሰላም መንገድ አምልኮአቸውን እንዲፈጽሙ የሚመለከተው የመንግሥት አካል የበኩሉን መመሪያ እንዲሰጥልን ቅዱስ ሲኖዶስ ይጠይቃል፡፡
3. ይህ ደም የማፍሰስና ሕይወትን የማጥፋት ተልእኮ አልበቃ ብሎ በየምክንያቱ የታሰሩ ካህናትና ምእመናን ወጣቶችም ጭምር በእስር ላይ መሆናቸው ስለሚታወቅ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከእስራት እንዲፈቱ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ አጥብቆ ይጠይቃል፡፡
4. ሀ. ከቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግና ደንብ ውጭ በመነሳሳት የኦሮምያ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እናቋቁማለን በማለት በሕገ ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ እንዲሁም በቅዱስ ሲኖዶስ ተባርኮ ጽላት ተሰጥቶናል በሚል በምድረ አሜሪካ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም ቤተ ክርስቲያን አቋቁመናል የሚሉት፡- (1) ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን (2) አባ ገ/ማርያም ነጋሳ (3) መምህር ኀ/ሚካኤል ታደሰ (4) ቄስ በዳሳ ቶላ፣ እነዚህ ግለሰቦች ቤተ ክርስቲያናችን በማታውቀው መንገድ በዐመፅ በመነሳሳት ምእመናንን ግራ እያጋቡና እያሳሳቱ መሆኑን እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ውጭ የክህደት ትምህርት ማስተማራቸው በመረጃ ተደግፎ ለቅዱስ ሲኖዶሱ ጉባኤ የቀረበ በመሆኑ እነዚሁ ከላይ ስማቸው የተጠቀሰ የኦሮምያ ቤተ ክህነት አደራጆች ነን የሚሉ ከድርጊታቸው ተቈጥበው በንስሓ እስኪመለሱ ድረስ ከየካቲት 11 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ከቤተ ክርስቲያናችን የተሰጣቸው ክህነት ተይዟል፡፡ በቤተ ክርስቲናያናችንም ስም ምንም ዐይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉና መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳይሰጡ ታግደዋል፡፡ ግለሰቦቹ ከጥፋት ድርጊታቸው ተፀፅተው ለመመለስ ከፈቀዱ ጉዳያቸው በድጋሚ እንዲታይ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
ለ. እነዚሁ ካህናት ነን የሚሉ ግለሰቦች በቅዱስ ሲኖዶስ ተባርኮ የተሰጠን ጽላት አለ በሚል ምእመናንን እያደናገሩ ቢሆንም እንደ ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዐትና ደንብ መሠረት ጽላት እንዲሰጣቸው ያልጠየቁ ከቤተ ክርስቲያናችንም የሰጣቸውም አካል አለመኖሩ በጉባኤው የተረጋገጠ በመሆኑ ምእምናን ከእንደዚህ ዐይነት ተሳስተው ከሚያሳስቱ ግለሰቦች ራሳቸውን ሃይማኖታቸውንና የቤተ ክርስቲያን ሥርዓታቸውን ከምንጊዜውም በላይ እንዲጠብቁ ጉባኤው አሳስቧል፡፡
5. በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በርካታ ቅዱሳንና መናንያን ለአገርና ለወገን የሚጸልዩባቸው ታላላቅ ገዳማት እንዳሏት ይታወቃል፡፡ ሆኖም ከጥቂት ዓመታት ወዲህ በአንዳንድ ገዳማት ላይ ግለሰቦች እያደረሱ ያለው ፈተናና ችግር ያለ መሆኑ ሲታወቅ በተለይም በአሁኑ ጊዜ፡-
ሀ. በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሊበን ዝቋላ ወረዳ የሚገኘው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም፣
ለ. በሰላሌ ሀገረ ስብከት በታላቁ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሆን ተብሎ በአንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች አማካኝነት እየደረሰ ያለው ችግር እና ታሪክን የማጠልሸት ሂደታቸው በአስቸኳይ እንዲቆም የሚመለከተውም የመንግሥት አካል ለጉዳዩ ትኵረት ሰጥቶ ችግር ፈጣሪዎችን እንዲያስቈም ለገዳማቱም የአገር ቅርስ እንደመሆናቸው ሁሉ አስፈላጊውን ጥበቃ እንዲያደርግ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነውን ውሳኔ መንግሥት እንዲያስፈጽምልን እንጠይቃለን፡፡
6. በዐረብ ኤምሬቶችና በዱባይ በስደት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያን ወገኖቻችን ከፈጣሪያቸው ጋር የሚገናኙበት እግዚአብሔርን የሚያመልኩበት ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት የአገሪቱ መንግሥት ከቤተ ክርስቲያናችን የቦታ ጥያቄ እየቀረበለት ምላሽ ሳናገኝ እስከአሁን ቆይተን ነበር፡፡ በአሁኑ ጊዜ ግን የአገራችን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በዐረብ ኤምሬቶች ባደረጉት የሥራ ጒብኝት በዚያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ዜጎቻቸውን ከማነጋገርና ከማጽናናት ባሻገር ከሀገሪቱ መንግሥት በመነጋገር ለክርስቲያን ወገኖቻችን የማምለኪያ ቤተ ክርስቲያን መሥሪያ ቦታ በማስፈቀዳቸው ከዚህም ጋር በዐረቡ ዓለም በስደት ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ከስደት እንዲመለሱና ለአገራቸው እንዲበቁ በማድረጋቸው ስደተኛ የሆኑ ክርስቲያን ወገኖቻችን በእጅጉ ያስደሰተና ቤተ ክርስቲያናችንም ሐዋርያዊ ተልእኮዋን እንድታስፋፋ የሚያግዝ በመሆኑ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በእጅጉ ከመደሰቱም በላይ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደዚህ ሀገራዊ መንበረ ሥልጣን ከተጠሩበት ጊዜ ጀምሮ የቤተ ክርስቲያናችንን ጉዳይ ጉዳያቸው አድርገው እየፈጸሙት ያለ አኵሪ መንፈሳዊ ተግባር ሁኖ ስላገኘው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የከበረ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡
7. በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን፡- በ“OMN”፣ በ“LTV”፣ በ“OBS” ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ በጥንታዊትና ሐዋርያዊት በሆነችዋ ለአገርና ለወገን ባለውለታና ባለ ታሪክ በሆነችው ቤተ ክርስቲያናችን የከፈቱት የስም ማጥፋት ዘመቻ ማካሄዳቸው ታሪክን እያበላሹ የተሳሳተ መረጃ ለሕዝብ ማስተላለፋቸው ከዚህም የተነሣ ከ60 ሚሊዮን ያላነሰ ተከታይ ያላትን ቤተ ክርስቲያን ክብሯንና ልዕልናዋን ዝቅ ባደረገ መልኩ የሚያስተላልፉት የተሳሳተ መረጃ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ብቻ ሳይሆን አገራዊ ቀውስ ለማምጣት እየተደረገ ያለ ጥረት በመሆኑ የሚመለከተው የመንግሥት አካል አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ የጣቢያዎቹ ኀላፊዎች ከብዙኃን መገናኛ ሕግ እና ደንብ አኳያ በሕግ እንዲጠየቁ ለወደፊቱም ከእንዲህ ዐይነት ሕገ ወጥ ድርጊት እንዲታቀቡ መንግሥትም በዚሁ ላይ አስፈላጊውን ውሳኔ እንዲያሳልፍልን ቅዱስ ሲኖዶስ ጠይቋል፡፡

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ከየካቲት 9-11 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ ለ3 ተከታታይ ቀናት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ከዚህ በላይ በተገለጹት ነጥቦች ላይ ከመከረና ውሳኔ ካሳለፈ በኋላ በኢትዮጵያ አገራችን በመንግሥትና በሕዝቡ ጭምር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ማለትም ሕዝባዊ አንድነት እንዲጐለብት፣ ማኅበራዊና ልማታዊ ተግባራት እንዲፋጠኑ፣ በአጠቃላይ በአገራችን ሰላምና አንድነት ሰፍኖ አገራችን ኢትዮጵያ መላው ዜጋ ከሚመኝላት የእድገት ጫፍ እንድትደርስ እንደ አንድ ልብ መካሪና እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆኖ ለሀገሩና ለሕዝባዊ አንድነቱ ጸንቶ እንዲቆም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ጥሪውን በማስተላለፍ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት በጸሎት ዘግቷል፡፡

እግዚአብሔር ሀገራችንን ኢትዮጵያን ይባርክ ቤተ ክርስቲያናችንን ይጠብቅ ለሕዝባችንም አንድነቱንና ሰላሙን ይስጥልን፣አሜን፤

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32020-02-19 09:48:512025-01-27 09:50:25የካቲት 11 ቀን 2012 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የእነ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን ሥልጣነ ክህነት በውሳኔ ማገዱን ቅዱስነታቸው እንደሚከተለው ገልጸዋል፡፡
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጥር 11 ቀን 2012 ዓ.ም የጥምቀት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥር 11 ቀን 2012 ዓ.ም የጥምቀት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥር 11 ቀን 2012 ዓ.ም የጥምቀት በዓል ቃለ ምዕዳንና... Link to: የካቲት 16 ቀን 2012 ዓ.ም የዐቢይ ፆም መግቢያ መልእክት Link to: የካቲት 16 ቀን 2012 ዓ.ም የዐቢይ ፆም መግቢያ መልእክት የካቲት 16 ቀን 2012 ዓ.ም የዐቢይ ፆም መግቢያ መል...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top