• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ከጥቅምት 12 እስከ 26 ቀን 2007 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡

November 5, 2014

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ስብሰባ፤ በዓመት ሁለት ጊዜያት እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 164 በተደነገገው መሠረት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የዘንድሮውን መደበኛ ስብሰባ ከጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ሲያካሂድ ሰንብቷል፡፡ በዚሁ መሠረት የመክፈቻው ሥርዐተ ጸሎት ከተፈጸመበት ከበዓሉ ዋዜማ ከጥቅምት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ጥቅምት 26 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ ለ15 ቀናት ያህል ባደረገው ጉባኤ ጠቀሜታ ባላቸው የአጀንዳ ነጥቦች ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፎአል፡፡ ከተላለፉት በርካታ ውሳኔዎች መካከልም ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡

1. የጥቅምቱ 2007 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በቅዱስ ፓትርያርክ የመግቢያ ንግግር ከተከፈተ በኋላ ሠላሳ ሦስተኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ያቀረበው የጋራ መግለጫ የ2007 የበጀት ዓመት የሥራ መመሪያ ሆኖ እንዲሠራበት ወስኗል፡፡

2. በቅዱስ ሲኖዶስ የተሠየመው አርቃቂ ኮሚቴ ያቀረበው ረቂቅ ሕገ ቤተ ክርስቲያን፤ ለምልአተ ጉባኤ ቀርቦ ገጽ በገጽ ከተነበበና እርማት ከተደረገ በኋላ ይኸው ሕግ እንዲሠራበት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በሙሉ ድምፅ ተስማምቶ አጽድቋል፡፡

3. የግንባታው ሥራ እየተካሄደ ለሚገኘው ለታላቁ የዐባይ ሕዳሴ ግድብ ማከናወኛ አገልግሎት ይውል ዘንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀደም ሲል ከሃያ ሦስት ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ማድረጓ የሚታወስ ነው፤ አሁንም ለሁለተኛ ጊዜ ከጠቅላይ ቤተ ክህነትና ከየአህጉረ ስብከቱ ጽ/ቤቶች የተገኘውን በድምሩ ብር 16,403,091.01 (ዐሥራ ስድስት ሚሊዮን አራት መቶ ሦስት ሺህ ዘጠና አንድ ብር ከዜሮ አንድ ሳንቲም) ገቢ ያደረግን ስለሆነ ይኸው ታውቆ የሕዳሴው ግድብ ለሀገራችን የእድገት ታሪክ ምዕራፍ ከፋች ይሆናል ተብሎ ስለታመነበት ሁሉም ኅብረተሰብ ጠቀሜታውን ከወዲሁ በበለጠ በመረዳት አስፈላጊውን ሁሉ በመፈጸምና በማስፈጸም እንዲረባረብ በዚህ አጋጣሚ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

4. በአሁኑ ጊዜ በዓለማችን በተለይም በምዕራብ አፍሪካ ዙሪያ እየቀሠፈ የሚታየው ‹‹ኢቮላ›› በመባል የሚታወቀው አዲስ ቀሣፊ በሽታ ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ እንዳይገባና ከዓለም ዙሪያ እንዲጠፋ ከወዲሁ መከላከል አስፈላጊ በመሆኑ ኅብረተሰቡ በመከላከሉ ረገድ ብርቱ ጥንቃቄ ያደርግ ዘንድ በመገናኛ ብዙኃን ሲነገር ይደመጣል፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም የኅብረተሰቡ አገልጋይ ከመሆኗ አንጻር የበኩሏን ድርሻ ልትወጣ የሚገባት ስለሆነ፤ በየአህጉረ ስብከቱ በየአንዳንዱ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ጸሎተ ምሕላ ይደረግ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያን ሰጥቷል፡፡

5. በጀትን በተመለከተ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ለ2007 ዓ.ም. ተጠንቶ የቀረበውን በጀት አጽድቋል፡፡

6. የሰዎች ሕገ ወጥ ዝውውር የሀገርን ክብር የሚፈታተን ተተኪ ትውልድን የሚያሳጣ ድርጊት በመሆኑ ይህን ሕገ ወጥ አሠራር ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትኲረት ሊሰጥበት እንደሚገባ እየተነገረ ነው፤ቤተ ክርስቲያኒቱም ቅድሚያ ለሀገርና ለወገን ክብር በመስጠት ይህን በተመለከተ በማንኛውም የቤተ ክርስቲያኒቱ ዐውደ ምሕረት ሁሉ አስፈላጊው ትምህርት እንዲሰጥ ወስኗል፡፡

7. በጋምቤላና በቤንች ማጂ ክልል በነዋሪው ሕዝብ መካከል ስለተከሠተው አለመግባባት ጉዳይ ምልአተ ጉባኤው ተነጋግሮ ለሀገሪቱ ሰላም ለልማትና ለእድገት ዕንቅፋት የሚሆኑ ጉዳዮች እንዲወገዱ፣ ኅብረተሰቡ በሰላምና በመግባባት እንዲኖር የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡

8. ከሀገር ውጭ ከሚገኙ የሃይማኖት አባቶች ጋር ተጀምሮ የነበረው ዕርቀ ሰላም ተጠናክሮ መቀጠሉ ለቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገር የሚበጅ መሆኑ ስለታመነበት አሁንም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስለ ቀጣዩ ሰላም በሰፊው ተነጋግሮ በቤተ ክርስቲያናችን በኩል የሰላሙ ሂደት ተጠናክሮ እንዲቀጠል ጉባኤው ወስኗል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ ውይይቱን በመቀጠል፤ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ጠብቆ በማስጠበቅ፤
– በቤተ ክርስቲያኒቱ ማእከላዊ አስተዳደር አመራር ሰጭነት የተጀመሩት ልዩ ልዩ የልማት ድርጅቶች ለውጤት በቅተው አገልግሎትን እንዲሰጡ ለማስቻል፤
– በሀገር ውስጥና በውጭው አህጉረ ስብከት ተመድበው በሚሠሩ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አማካይነት የተካሄደውን ሐዋርያዊ ተግባር በመገምገም፤
– ጧሪ ቀባሪ የሌላቸው አረጋውያንና አረጋውያት የሚጦሩበት፤ አሳዳጊ የሌላቸው ሕፃናት እየተማሩ የሚያድጉበት የምግባረ ሠናይ ተቋማት በየአህጉረ ስብከቱ እንዲቋቋሙ ለማድረግ፤
– ለሀገራችን ኢትዮጵያና ለቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ እድገትና ልማት የሚበጀውን ሁሉ መፈጸም የሚያስችል መመሪያን ሰጥቶ ስብሰባውን በጸሎት አጠናቋል፡፡

እግዚአብሔር አምላካችን ሕዝባችንን ሀገራችንን ይባርክ፤ ለሀገራችን ለዓለሙ ሁሉ ሰላሙን ይስጥልን፤

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc2014-11-05 16:39:032024-12-04 16:42:37ከጥቅምት 12 እስከ 26 ቀን 2007 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ... Link to: ታኅሣሥ 29 ቀን የ2007 ዓ.ም የልደት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ታኅሣሥ 29 ቀን የ2007 ዓ.ም የልደት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ታኅሣሥ 29 ቀን የ2007 ዓ.ም የልደት በዓል ቃለ ምዕዳንና...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top