• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ሚያዝያ 24 ቀን 2013 ዓ.ም ቅዱስነታቸው የትንሣኤ በዓልን አስመልክተው የሰጡት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

May 2, 2021

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
በሕመም ምክንያት በየጸበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት ሁሉ፤

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ። የትንሣኤ በኲር፣ የሰላም መበሥር የሆነው ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ፡፡
“ወመጽአ እግዚእ ኢየሱስ ወቆመ ማእከሌሆሙ ወይቤሎሙ ሰላም ለክሙ
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጣ በመካከላቸውም ቆሞ ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው።”
(ዮሐ. 2ዐ፥19)፡፡

ይህ ቃል ቅዱሳን ሐዋርያት በኢየሩሳሌም ከተማ፣ቀራንዮ በተባለው ስፍራ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ በሆነው ነገር ሁሉ በኀዘንም በፍርሀትም ተውጠው በተዘጋ ቤት ውስጥ ሳሉ የተነገረ ቃለ ሰላም ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እሑድ እኩለ ሌሊት በኀይለ መለኮቱ ሞትንና መቃብርን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ ለማርያም መግደላዊትና ለሌሎች ቅዱሳት አንስት በመጀመሪያ ተገልጾአል፡፡ ቀጥሎም በኤማሁስ ለሁለት ደቀ መዛመርቱ ተገልጾላቸዋል& በዚህ ቀን አመሻሹ ላይ ደግሞ ሐዋርያት በጽርሐ ጽዮን ሳሉ በሩም መስኮቱም እንደተዘጋ በአምላክነቱ ኀይል ገብቶ በድንገት በመካከላቸው በመገኘት “ሰላም ለእናንተ ይሁን” ሲል የኋላ ኋላ የሕይወት ኀይል፣ የትንሣኤ ኀይል፣ የሰላም ኀይል አሸናፊ መሆኑን አብሥሮአቸዋል፡፡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከትንሣኤው በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ያሰማው ዐቢይ ኀይለ ቃል ሰላም ለእናንተ ይሁን የሚለው አጽናኝ ቃል ነው፡፡

በእርግጥም በዚያች ቀውጠኛ ሳምንት ለሐዋርያት ከሰላም የበለጠ የሚያስፈልጋቸው ሌላ ነገር አልነበረም፤ ምክንያቱም ቅዱሳን ሐዋርያት ሰላም ከማጣታቸው የተነሣ ዕለታዊ ተግባራቸው ከመቋረጡም በላይ ሕይወታቸውም ከባድ ሥጋት ላይ በመውደቁ በአንድ ቤት በመሰባሰብ በሩንም መስኮቱንም ክርችም አድርገው በመዝጋት ራሳቸውን መሠወር መርጠዋል፡፡ ታድያ በዚህ ጊዜ ነበረ የሰላም ባለቤት የሆነው መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ መጣ በዚህ ገባ ሳይባል መስኮቱና በሩ እንደተዘጋ ድንገት በመካከላቸው ተገኝቶ የሰላምን ቃል ያሰማቸው ቅዱሳን ሐዋርያትም አጥተውት የነበረውን የሰላም ድምፅ በመስማታቸው እጅግ ደስ አላቸው፤ ፍርሀታቸው ተወገደላቸው፤ ፍጹም ሰላምና ነፃነትም በውስጣቸው አበራ& የተማመኑበት ጌታ ሞትና መቃብር ይዘው የማያስቀሩት መሆኑን በተግባር ሲያዩ ጭንቀቱና ሥጋቱ ሁሉ ስፍራውን ለቀቀ፤ በምትኩም ደስታው፣ በጌታ መታመኑና ሰላሙ ውስጣቸውን ሞላው፤ ነገሮች በቅጽበት ተለዋውጠዋልና የተዘጋውን በር ራሳቸው ከፈቱት፤ ከዚህ ቀን ጀምሮ የጌታን ትንሣኤ ለመመስከርና ለዓለም ሁሉ ለማድረስ አንድ ብለው ጒዞውን ለመጀመር በልበ ሙሉነት ዝግጁ ሆኑ፤ የጌታችን መሰቀል መሞትና መነሣት በመመስከሩና በማስተማሩ ረገድ በዚህ ዓለም ሊገድባቸው የሚችል ኀይል እንደማይኖር እርግጠኞች ሆኑ፤ በአካላቸው ላይ ሊቃጣ የሚችል መከራ ሁሉ ከቊጥር ላለማስገባት በሕሊናቸው ደመደሙ፤ በሂደትም ይህንን በተግባር አሳዩ፣ ይህንን ሁሉ ድፍረትና ቈራጥነት የሰጣቸው ሌላ ሳይሆን የትንሣኤው ኀይል እንደ ነበልባለ እሳት ግሎ በልቡናቸው ውስጥ በመቀጣጠሉ ነበር፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት፤

ከጌታችን ትንሣኤ በፊት የነበረው ፍርሐትና ሥጋት ዛሬም ከዓለማችን አልወጣም፤ ዛሬም ሰዎች ውስጣዊም ሆነ ውጫዊ ሕይወታቸው በፍርሀት በጭንቀትና በሥጋት እንደተከበበ ነው፡፡ ዛሬም ልክ ሐዋርያት እንደነበሩበት ዝግ ቤት ቤታቸውን የዘጉ፣ አሊያም ጥለው የሸሹ፣በመካከላቸውም ሕይወታቸውን ያጡ፣ሕይወታቸው ቢተርፍም የሚላስ፣ የሚቀመስ፣ የሚጐረስ፣ የሚለበስ፣ ያጡ ብዙ ናቸው፡፡ ከዚህ አኳያ ሰዎች ነንና ይህ ለምን ሆነ ብለን ልንጠይቅ ተፈጥሮና ሃይማኖት ያስገድዱናል፤ መልሱ ግን አንድና አጭር ነው፡፡ እሱም ሰላም በመጥፋቱ ነው፡፡ ይህንን ሰላም ያጣነው በሌላ ሳይሆን በእኛው በራሳችን ነው፤ መፍትሔ የሌለው ነገር ያለ ይመስል ቁጭ ብለን በአንድነትና በጋራ ተወያይተን ችግራችንን መፍታት አቅቶን ያመጣነው ጣጣ ነው፡፡ እንግዲህ እግዚአብሔር የሰጠንን ብሩህ አእምሮ ተጠቅመን የራሳችንን ችግር በራሳችን መፍታት ካልቻልን በማንም ይሁን በማን ብናመካኝ የሚቀበለን አናገኝም፤ እግዚአብሔር እንደሆነ በተፈጥሮም ሆነ በቅዱስ መጽሐፉ የሰላም መገኛዋና መጠበቂያዋ ዕርቅና ይቅርታ እንደሆነ ባለማወላወል ነግሮናል፡፡ እሱ ያለውን የማንቀበል ከሆነ እኛን በሚቀጣበት ሥልጣኑ ቀጥቶ በኀይለ መለኮቱ ሰላሙን ለድሆቹ ፍጡራን ያጐናጽፋል&ይህ የእግዚአብሔር አሠራር ስለሆነ እሱም አያልፈውም እኛም አናስቀረውም፤ ነገር ግን ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚመክረን እሱ ሳይፈርድብን በይቅርታና በዕርቅ እኛው በእኛው ላይ ብንፈርድ ትልቅ ጥበብና ብልኅነት ነው&አሁንም የእኛ ቀን የጨለመ ቢመስልም ለእግዚአብሔር ቀኑ ሁሉ አይጨልምምና ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን እባካችሁ ሁሉን ነገር እርግፍ አድርገን በመተው ለዕርቅና ለሰላም፣ ለይቅርታና ለአንድነት፣ ለእኩልነትና ለወንድማማችነት ያለ ማቋረጥ ብንተጋ መልካምና ጣፋጭ የሕይወት እሸት እንቀምሳለን፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት፤

የሰው ልፋት ምንም ቢበዛ እግዚአብሔር ካልፈቀደው የሚሆን እንዳልሆነ የምንዘነጋው አይደለም፤ እግዚአብሔርን ፊት ለፊታችን አድርገን የማንሠራው ሥራ ሁሉ ብላሽ እንደሆነ የምንገነዘበው እግዚአብሔርን ከፊት ለፊታችን ገለል አድርገን ለብቻችን የሮጥንባቸው የዓመታት ጒዞ የት እንዳደረሱን በአእምሮአችን አስተውለናል& በዓይናችንም አይተናል፣ በጆሮአችን ሰምተናል፤ ከእግዚአብሔር ኮብልለን ማምለጥ እንደማንችልም ከኛ በላይ ሌላ ምስክር አያስፈልገንም&ለእኛ ያሉን ተመራጭና ብቸኛ ዕድሎች እግዚአብሔርንና ሰላም፣አንድነትና እኩልነት፣ ዕርቅና ይቅርታ ብቻ ናቸው፡፡ ከዚህ ውጭ ምንም ተመራጭ ዕድል የለንም&ጌታችንም በትንሣኤው ዕለት ሰላሙን በቃለ ብሥራት ያበሠረን ከሰላም የተሻለ እኛን የሚጠቅም ሌላ አማራጭ እንደሌለ ስለሚያውቅ ነው፡፡

በመጨረሻም በዓለ ትንሣኤውን ስናከብር በሰላም ዕጦት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በየመጠለያው የሚገኙ ልጆቻችንና ወገኖቻችንን በመመገብ፣ በማጠጣትና&በማልበስ ከኛ ጋር የፋሲካውን በዓል በመጽናናት እንዲያሳልፉ ሁሉም ሕዝበ ክርስቲያን የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ፣ ከዚህ ጐን ለጐንም ሰላም እንዲሰፍን የሰላም ኀይሎች ሁሉ የበኩላቸውን ጥረት እንዲያደርጉ፣እግዚአብሔርንም ለሰላማችን መረጋገጥ መለኮታዊ ሥራውን እንዲሠራ እንድንማፀነው አባታዊና መንፈሳዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

መልካም በዓለ ትንሣኤ ያድርግልን!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32021-05-02 14:12:472025-01-28 14:13:43ሚያዝያ 24 ቀን 2013 ዓ.ም ቅዱስነታቸው የትንሣኤ በዓልን አስመልክተው የሰጡት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ.ም የዓብይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ.ም የዓብይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ.ም የዓብይ ጾምን መግባት በማስመልከት... Link to: ግንቦት 18 ቀን 2013 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ግንቦት 18 ቀን 2013 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ግንቦት 18 ቀን 2013 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top