• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

የካቲት 12 ቀን 2009 ዓ.ም የዐቢይ ጾም መግቢያ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ።

February 19, 2017

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤
በሀገር ውስጥና በመላው ክፍላተ ዓለም የምትገኙ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፤

ፍጥረቱን በምሕረት፣ በይቅርታና በርኅራኄ የሚጠብቅ፣ የሚመግብና የሚያስተዳድር፣ ከሁሉ በላይ የሆነ ኀያሉ አምላካችን እግዚአብሔር እንኳን ለሁለት ሺሕ ዘጠኝ ዓመተ ምሕረት መዋዕለ ጾም ዐቢይ በሰላም አደረሳችሁ።

“ቅረቡ ኀቤሁ ወያበርህ ለክሙ፣ ወኢይትኀፈር ገጽክሙ
ወደ እርሱ ቅረቡ ያበራላችኋልም፤ ፊታችሁም አያፍርም”፡፡”
(መዝ. 34፥5)

የሰው ልጅ ከአራቱ ባሕርያተ ፍጥረት በተገኘ ሥጋዊ ሕይወቱ፣ የአራቱ ባሕርያት ውጤት የሆኑትን ማለትም እህልን ውኃን፣ ነፋስንና እሳትን የመሻት ፍላጎቱ የላቀ እንደሆነ ሁሉ፣ ከእግዚአብሔር በተገኘ መንፈሳዊ ሕይወቱም እግዚአብሔርን የመሻት ፍላጎቱ ከፍተኛ ነው፤ ከእግዚአብሔር የተገኘው ይህ ሀብተ ተፈጥሮ ከሰው ባሕርይ መለየት የማይቻል በመሆኑ ሰብኣዊ ፍጡር ሁሉ ከፈጣሪው ጋር ግንኙነት ለማድረግ ይጓጓል፡፡

ሰው ወደ ፈጣሪው ለመቅረብ ከሚፈልገው በላይ፣ ፈጣሪም ሰውን በእጅጉ ሊቀርበውና ማደርያው ሊያደርገው ይፈልጋል፤ በመሆኑም ሁለቱም ተፈላላጊ መሆናቸውን በሕገ ተፈጥሮም ሆነ በቅዱስ መጽሐፍ የታወቀ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ሁለቱም እንዳይቀራረቡ የሚያደርጉ መሠረታውያን ነገሮች እንዳሉ ሁሉ እንዲቀራረቡ የሚያደርጓቸውም አሉ፤ ሁለቱንም ሊያቀራርቡ ከሚችሉት መካከል አንዱ ጾም ነው፡፡ እግዚአብሔር በሁለመናው ንጹሕ ቅዱስ ፍጹምና ክቡር በመሆኑ ለባሕርዩ ከማይስማሙ ድርጊቶችና ከአድራጊዎቻቸው ጋር ግንኙነት ሊያደርግ አይፈቅድም፤ ሆኖም ንስሓ ሲገቡና ጥፋታቸውን አምነው ሲፀፀቱ በይቅርታ የሚቀበል ርኅሩኅ መሓሪና ይቅር ባይ አምላክ ነው፤ ከዚህ አኳያ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የሚፈጠረውን ክፍተት ለማጥበብ ብሎም ለመዝጋት ንስሓ ጾምና ጸሎት ቊልፍ መሣሪዎች ናቸው፤ እኛ ክርስቲያኖችም ጾምን የምንጾምበት ዋና ምክንያት ይኸው ነው፡፡

ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ መንፈሳዊ ኀይል ያስፈልጋል፤ መንፈሳዊ ኀይል የሚገኘው ደግሞ ሥጋዊ ኀይል ሲገታ ነው፡፡ ጾም ይህንን በማድረግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ ጾም ኀይለ ሥጋን በመግራት ኀይለ መንፈስ እንዲበረታ ያደርጋል፣ ጾም ራሳችንን ዝቅ አድርገን ለእግዚአብሔር እንድንገዛና ለቃሉ ታዛዥ እንድንሆን ያስችለናል፤ ጾም ሰከን ብለን ስለበደላችን እንድናስብና ለንስሓ እንድንፈጥን ያደርገናል፣ ጾም የእግዚአብሔርን ቸርነት በማሰብ ፍቅሩን እንድናውቅና እንድናመልከው፣ ለሰውም ጥሩ የሆነውን ብቻ እንድናስብ ያደርገናል፡፡ እነዚህ ነገሮች በሕይወታችን ውስጥ ሥርጸት ሲያገኙ ወደ እግዚአብሔር የመቅረቡና የመገናኘቱ ዕድል ሰፊ ይሆናል፡፡ በዚህ ሕይወት ውስጥ ሆነን ስለምንሻው ነገር እግዚአብሔርን ብንጠይቅ መልሱ ፈጣን ይሆናል፤ ከዚህ አንጻር የነነዌ ጾም ያስገኘው ፈጣን መልስ ማስረጃችን ነው፤ በጾም ኀይል አማካኝነት ከፈጣሪ ጋር የተገናኙ እነ ሊቀ ነቢያት ሙሴ፣ ነቢዩ ዳንኤልና ዕዝራም በዚህ ተጠቃሽ መምህሮቻችን ናቸው፡፡ ርኵስ መንፈስን ድል ለማድረግ፣ ሊጀመር የታሰበውን ዐቢይ ተግባር በስኬት ለማጠናቀቅ በጾም ረድኤተ እግዚአብሔርን መጠየቅ አስፈላጊ መሆኑን ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተገባርና በትምህርት አሳይቶናል፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያትም ይህንን በተግባርና በትምህርት ፈጽመውታል፤ ከዚህ አኳያ ጾምና ሃይማኖት የማይለያዩ የአንድ ሣንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን መገንዘብ አያዳግትም፡፡ በመሆኑም ጾም ራሳችንን ለመቈጣጠር፣ የእግዚአብሔር ታዛዥ ለመሆን፤ ለጥያቄአችን ፈጣን መልስ ለማግኘት፤ ርኵስ መንፈስን ድል ለማድረግ፤ ከእግዚአብሔር ጋር ለመገናኘት የሚያገለግለን ሃይማኖታዊና መንፈሳዊ መሣሪያ ነው፡፡

የጾም አስፈላጊነትና ውጤታማነት ከጥንት ጀምሮ በነቢያትና በሐዋርያት የታወቀ፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ እግዚአብሔር ራሱ “በፍጹም ልባችሁ፣ በጾም፣ በልቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ፣ ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ፤ አምላካችሁ እግዚአብሔር ቸርና መሓሪ ነው፤ ቊጣው የዘገየ ምሕረቱ የበዛ ለክፋትም የተፀፀተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ፤ በጽዮን መለከትን ንፉ፤ ጾምንም ቀድሱ (ለዩ) ጉባኤውንም አውጁ፤ ሕዝቡንም አከማቹ፤ ማኅበሩንም ቀድሱ” ብሎ ጾምን በአዋጅ እንድንጾም አዞናል (ኢዩ. 2፥12-18)፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ርኵስ መንፈስ ሊሸነፍና ድል ሊሆን የሚችለው በጾምና በጸሎት እንደሆነ አስረግጦ አስተምሮናል፤(ማቴ. 17፥14-21) ይሁንና ጾም በእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋም፣ መልስም፣ ኀይልም ሊያሰጥ የሚችለው እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ማለትም እግዚአብሔር ባዘዘው ትእዛዝ መሠረት ሲከናወን መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፤ እግዚአብሔር የሚፈልገው ጾም እንዴት ያለ እንደሆነ እርሱ ራሱ እንዲህ ብሎናል “እኔ የመረጥሁት ጾም ይህ አይደለምን? የበደልን እስራት ትፈቱ ዘንድ፣ የቀንበርን ጠፍር ትለቁ ዘንድ፣ የተገፉትን አርነት ትሰዱ ዘንድ፣ ቀንበሩን ሁሉ ትሰብሩ ዘንድ አይደለምን ? እንጀራህን ለተራበ ትቈርስ ዘንድ፣ ስደተኞቹ ድሆችን ወደቤትህ ታገባ ዘንድ፣ የተራቈተውን ብታይ ታለብሰው ዘንድ፣ ከሥጋ ዘመድህ እንዳትሸሸግ አይደለምን? የዚያን ጊዜ ብርሃንህ እንደ ንጋት ያበራል ፈውስህም ፈጥኖ ይበቅላል፤ ጽድቅህም በፊትህ ይሄዳል፤ የእግዚአብሔርም ክብር በላይህ ሆኖ ይጠብቅሃል” ብሎ ፈቃዱን ነግሮናል፡፡ (ኢሳ. 58፥6-8)

የጾም ዐቢይ ዐላማ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና የተሰበረን ልብ መፍጠር፣ በጾም በጸሎት በንስሓ በስግደት በተመሰጦ፣ በአንቃዕድዎ ለእርሱ መታዘዝና መገዛት እርሱንም ማምለክ ነው፡፡ ከዚህም ጋር ጥልን በይቅርታ ማስወገድ፣ ሰላምን በማረጋገጥ ፍቅረ ቢጽን ገንዘብ ማድረግ፣ ራስን መቈጣጠርና መግዛት፣ ኀይለ ሥጋን መመከት፣ ኀይለ ነፍስን ማጎልበት፣ የእግዚአብሔርን እንጂ የሰውን አለማየት፣ የርኩሳን መናፍስትን ግፊት በመቋቋም ክፉ ምኞትን ድል ማድረግ፣ ቅዱስ ቊርባንን መቀበል፤ ኅሊናን ለእግዚአብሔር መስጠት፣ ያለንን ለነዳያን ከፍለን መመጽወት የመሳሰሉትን ሁሉ ዕለታዊ ተግባራችን በማድረግ ጾሙን ልንጾም ይገባል፡፡

በመጨረሻም፡ የጾም ዋና ዐላማ ለእግዚአብሔር መታዘዝ እንደ መሆኑ መጠን ምድርን እንድናበጃትና እንድናለማት ያዘዘንን ትእዛዝ ተቀብለን አካቢያችንን በማልማት ሀገራችንን ውብና ለኑሮ የተመቸች በማድረግ እንደዚሁም ከኀጢአት መከላከያዎች መካከል ዋናውና አንዱ ያለ ዕረፍት በሥራ መጠመድ ነውና ሕዝቡ ሥራ ሳይፈታ ፈጣሪውን በጾም እያመለከ፣ የተቸገረ ወገኑን ካለው ከፍሎ እየረዳ፣ ልማትንም እያፋጠነ የሀገሩን ሰላምና ፀጥታ እየጠበቀ መዋዕለ ጾሙን እንዲያሳልፍ በእግዚአብሔር ስም መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡

ወርኀ ጾሙን አስፈጽሞ ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም ያድርሰን እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ይቀድስ፣ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32017-02-19 13:19:082025-01-28 13:20:23የካቲት 12 ቀን 2009 ዓ.ም የዐቢይ ጾም መግቢያ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ።
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጥር 11 ቀን 2009 ዓ.ም. በበዓለ ጥምቀት የተላለፈ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥር 11 ቀን 2009 ዓ.ም. በበዓለ ጥምቀት የተላለፈ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥር 11 ቀን 2009 ዓ.ም. በበዓለ ጥምቀት የተላለፈ ቃለ... Link to: መጋቢት10 ቀን 2009 ዓ.ም የደብረ ዘይት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: መጋቢት10 ቀን 2009 ዓ.ም የደብረ ዘይት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ መጋቢት10 ቀን 2009 ዓ.ም የደብረ ዘይት በዓል ቃለ ምዕዳንና...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top