• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ጥቅምት 11 ቀን እስከ 16 ቀን 2009 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡

October 26, 2016

በስመ አብ ወወልድ ለመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ፣ በዓመት ሁለት ጊዜያት እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቍጥር 164 በተደነገገው መሠረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የመክፈቻው ሥርዓተ ጸሎት ከተፈጸመበት ከጥቅምት 11 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ጥቅምት 16 ቀን 2009 ዓ.ም. ድረስ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባን በማካሄድ፣ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለኅብረተሰባችን የሚጠቅመውን፣ ለሀገርና ለዓለም ሰላም የሚበጀውን አጀንዳ በማመቻቸት በስፋትና በጥልቀት ተወያይቶ የሚከተለውን ውሳኔ አሳልፏል፡፡

“ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ ኀበ እግዚአብሔር – ኢትዮጵያ ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያውያት እጆቻቸቸውን ወደ እግዚአብሐር ይዘረጋሉ” ይላል ነቢየ እግዚብሔር ዳዊት (መዝ. 67፣31)

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ክፍለ ዓለም፣ በአፍሪካ ቀንድ በሰሜን ምሥራቅ አፍሪካ በዐባይ ሸለቆ ዙሪያ በቀይ-ባሕር አካባቢ የምትገኝ ሀገር ናት፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ የነፃነት፣ የአንድነት ዕድሜ የተቈጠረላት በዚህም ረዥም የነፃነትና የአንድነት ዕድሜዋ ብዙ አገልግሎት ያበረከተች ሰፊ ታሪክ ያስመዘገበች ሉዓላዊት ሀገር ናት፡፡

አገራችን ኢትዮጵያ ባሳለፈችው ረዥም ዘመኗ በርካታ ደጋግ መልካም ሥራና ስም የነበራቸው ታላላቅ ሰዎች አልፈውባታል፡፡ ለታሪኳ፣ ለቅርሷ፣ ለባህሏ፣ ለዕድገቷ፣ ለድንበሯ ለአንድነቷ፣ ለነፃነቷ፣ ለክብሯ በሚገርም ወኔና ጀግንነት ደማቸውን ያፈሰሱላት፣ አጥንቶቻቸውን የከሰከሱላት ጀግኖች እንደነበሩአት አሁንም እንዳሏት በታሪክ ተመዝግቧል፡፡ ይህም በመሆኑ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዘመናቸው እርስ በርሳቸው በመከባበር የተራበውን በማብላት፣ የተጠማውን በማጠጣት፣ የታረዘውን በማልበስ፣ ያለማውን በማልማት፣ ቤት የእግዚአብሔር ነው በሚል አገራዊ ትውፊት እንግዳ እየተቀበሉ እግር እያጠቡ ቤት ያፈራውን ተካፍለው በመብላት ተከባብረው በመኖር የታወቁ ደጋግ አባቶች ልጆች መሆናችን ይታወቃል፡፡

ሀገራችን ኢትዮጵያ የተለያየ ቋንቋ ተናጋሪ የኅብረተሰብ ክፍሎች ለአያሌ ዘመናት የኖሩባትና አሁንም የሚኖሩባት በአርኣያነት ልትጠቀስ የሚገባት ብቸኛ ሀገር መሆኗ ከማንም ግንዛቤ የተሠወረ አይደለም፡፡ ይሁንና በአሁኑ ጊዜ በሀገራችን፣ የሰዎች ሕይወት እየጠፋ መሆኑ፣ የአገር ሀብትና ንብረት እየወደመ መታየቱ፣ ከነበሩበት እና ከኖሩበት ቦታ የሕዝቦችን ፍልሰት ማስከተሉ፣ በእነዚህም እየታዩ ባሉ ችግሮች ምክንያት በሰላማዊው ኅብረተሰብ ዘንድ ከፍተኛ ሥጋት እየሰፈነ መምጣቱና ልማታዊ ሥራዎችም ሊስተጓጐሉ እንደሚችሉ መገንዘብ ተችሏል፡፡ ስለዚህ የዚሁ የጥቅምቱ 2009 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በአገሪቱ እየታየ ባለው የሰላም ችግር ላይ በሰፊው በመወያየትና በመነጋገር የሚከተለውን መግለጫ አውጥቷል፡፡

1ኛ. በአገራችን ውስጥ ለአገራችን ዕድገት ሲባል ምላሽ የሚያሻቸው ጥያቄዎች አሉን የሚሉ ወገኖች ሁሉ እንደ ጥንት አባቶቻችን ኢትዮጵያዊነትን በተላበሰ፣ በሰከነና በተረጋጋ ሁኔታ ጥያቄያቸውን ጉዳዩ ለሚመለከተው አካል እንዲያቀርቡ፣
2ኛ. መንግሥት በአንድ አገር ውስጥ ለሚኖሩና ለሚያስተዳድራቸው ዜጎች እንደቤት ኀላፊና ልጆቹን እንደሚያስተዳድር መሪ እንደመሆኑ መጠን በሰከነና በተረጋጋ መልኩ ከዜጎች የሚቀርቡ ጥያቄዎችን በአግባቡ በመፈተሽና በማጥናት ለአገርና ለወገን የሚጠቅመውን ምላሽ እንዲሰጥባቸው ለሕዝቡ የገባውንም ቃል በተግባር አውሎ በሥራ እንዲተረጐም፣
3ኛ. የነገድ፣ የሃይማኖትና የጾታ ልዩነት ሳይኖር ለጋራ ህልውና፣ ለጋራ ልማትና ለጋራ ብልጽግና ለሀገራችን ኢትዮጵያና ለጐረቤት አህጉር ብሩህ ተስፋ ሠንቆ እንደሚመጣ የተነገረለት የሕዳሴው ግንባታ ፕሮጀክት ኢትዮጵያዊነቱን እያስመሰከረ ስለሆነ እንዲሁም በዘመናችን የምንታወቅበት ዐቢይ ታሪካችን የዐባይ ሕዳሴ ግንባታ ግድብ የመሆኑን ያህል አሁንም ፕሮጀክቱ ተጠናክሮ ይቀጥል ዘንድ በማንኛውም አቅጣጫ በሁሉም ወገን ያለ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በአንድነት ለግንባታው በመሰለፍ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ፣
4ኛ. ባለፈው ዓመት በነበረው የዝናም እጥረት ምክንያት በአገራችን ደርሶ የነበረው ድርቅ በመንግሥትና በመላው ኢትዮጵያዊ ሙሉ ድጋፍ ያለምንም የውጭ ርዳታ ችግሩን መወጣታችን ይታወቃል፡፡ ሆኖም በቀጣዩ ዜጎችን ለረሀብና ለስደት የሚዳርግ እንዲህ ዐይነት አስከፊ አደጋ በአገራችን እንዳይከሠት አገራችን እግዚአብሔር ባደላትና በሚያድላት የተፈጥሮ ጸጋ ምድሪቱን እየተንከባከብን ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ለልማቱ በመነሣት ምርታማነትን በማሳደግ ለዕድገት እንድንበቃ ተግተን የሥራ ባህላችንን ልናዳብር ይገባል፡፡
5ኛ. ሥር ነቀል የግንባታ ሥራ እየተካሄደባት ያለች ሀገራችን ኢትዮጵያንና ጥቅሞቿን በማይጻረር በሰላማዊ መንገድ ተቀራርቦ በክብ ጠረጴዛ የጋራ ውይይት በማካሄድ ችግሮችን መፍታት አግባብነት ያለው አሠራር ስለሆነ የሀገር ጉዳይ የጋራና የውስጥ ጉዳይ እንጂ ድንበር ተሻጋሪ እንዳልሆነ በአገሪቱ የሚገኙ የፖለቲካ ተቃዋሚዎች ግንዛቤን ወስደው የበኩላቸውን ድርሻ መፈጸም ይችሉ ዘንድ የራሳቸው የሆነውን አመለካከት ይዘው ሀገሪቱን ከሚመራው መንግሥት ጋር በክብ ጠረጴዛ እንዲወያዩ፣
6ኛ. ቀደምት አበው ኢትዮጵያውያን ዐረፍተ ዘመን እስከገታቸው ድረስ ሀገራቸውን ጠብቀው ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ታሪክ ለቀጣዩ ታሪክ ተረካቢ ትውልድ ማቆየታቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ወጣቱ ትውልድ ከቀደምት አበው የወረሰውን ትውፊት በመከተል፡- ለሀገራችን የሚጠቅሙትን፣ ለልማትና ለሰላም የሚበጁትን፣ በሀገር ውስጥ ያሉ እና ከሀገር ውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን አንድነትና ኅብረት የሚጠናከርበትን ሁኔታ በመሻት የበኩሉን ድርሻ ማበርከት ይጠበቅበታል፡፡
7ኛ. አገራችን ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ራሷን ከወራሪ ጠላት በመከላከል ነፃነቷንና ክብሯን፣ ሰላሟንም ጭምር ጠብቃ ይዛ የቈየች መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን በየዘመናቱ የውጭ ወራሪዎችና ጣልቃ ገቦች አገጣሚዎችን እየተጠቀሙ ሕዝቧን ሰላም ለመንሳት ሙከራ ሲያደርጉ እንደቈዩና በመንግሥትና በሕዝቡ አንድነት አስፈላጊው አገራዊ ጥበቃ እየተደረገ ሳየሳካላቸው በነፃነት ኑራለች፡፡ አሁንም በአገራችን እየታየ ያለው የሰላም መታጣት አንዳንድ የውጭ ጣልቃ ገቦች እጅ እንዳለበት በርካታ አመላካች ሁኔታዎች እየታየ ሲሆን እነዚህ ከአገራችን ውጭ በአገራችን ጉዳይ ጣልቃ የሚገቡ ሰላም የሚነሱ የውጭ ዜጎች ከአጥፊ ተልእኳቸው እንዲገቱ ቤተ ክርስቲያን አጥብቃ በማሳሰብ ድርጊቱን ትቃወማለች፡፡
8ኛ. ቤተ ክርስቲያናችን ለአገራችን ኢትዮጵያና ለሕዝቦቿ ባለውለታ በመሆን ሕዝቡን የሰላም ወንጌል በማስተማር የተጣላ በማስታረቅ የተለያየውን አንድ የማድረግ ተልእኮዋን በመፈጸም የቈየች እንደመሆኗ አሁንም ዕለት በዕለት ከምታከናውነው መንፈሳዊ አገልግሎት ባልተናነሰ መልኩ ከቅዱስ ሲኖዶሱ ጀምሮ እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በሕጓና በሥርዐቷ መላው ካህናትና አገልጋዮች በዕለተ ሰንበት ለሚገኘው ሕዝበ ክርስቲያን፣ በማታ ጉባኤ፣ በወርኃዊና ዓመታዊ በዓላት ሁሉ ሕዝበ ክርስቲያኑ በሥነ-ምግባር ታንጾ በፈረሃ እግዚአብሔር በግብረ-ገብነት ለአገሩ ሰላምና ለሕዝቡ አንድነት ተባብሮ እንዲቆም የሚያስችል ትምህርት እንዲሰጡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መመሪያን ያስተላልፋል፣
9ኛ. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ እስከዛሬ ባደረገው ስብሰባ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ተዘጋጅቶ በቀረበው የ2009 ዓ.ም. በጀት ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል፡፡
10ኛ. ከጥቅምት 7-10 ቀን 2009 ዓ.ም.በተካሄደው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የቀረበው የጋራ መግለጫ ላይ ተወያያቶ አንዳንድ ማሻሻዎችን በማድረግ የ2009 ዓ.ም. በጀት ዓመት የሥራ መመሪያ በማድረግ አጽድቋል፡፡
11ኛ. ለተዋሕዶ ሃይማኖታቸው ለሀገራቸው ልዕልናና ነፃነት በ1928 ዓ.ም.ከአርበኞች ጎን በመሆን ለሀገራቸው ነፃነት ጠንክረው እንዲዋጉ ሲያስተምሩ በነበረበት ወቅት በኢጣልያ ፋሽስታዊ መንግሥት በጎሬ ከተማ በ1929 ዓ.ም. በግፍ በሰማዕትነት የተገደሉት ብፁዕ አቡነ ሚካኤል ሰማዕት ተብለው እንዲጠሩ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ወስኗል፡፡
12ኛ. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ከጥቅምት 12- 16 ለአምስት ቀናት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ከላይ በተጠቀሱትና በሌሎችም በቤተ ክርስቲያኒቱ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ሲወያይ ሰንብቶ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት አጠናቋል፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32016-10-26 08:56:322024-12-07 09:00:57ጥቅምት 11 ቀን እስከ 16 ቀን 2009 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2009 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2009 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥቅምት 12 ቀን 2009 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ... Link to: ታኅሣሥ 29 ቀን 2009 ዓ.ም የልደት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ታኅሣሥ 29 ቀን 2009 ዓ.ም የልደት በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ታኅሣሥ 29 ቀን 2009 ዓ.ም የልደት በዓል ቃለ ምዕዳንና...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top