• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 25 ቀን 2015 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡

November 4, 2022

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜያት እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቍጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልአተ ጉባኤው የመክፈቻውን ሥርዓተ ጸሎት ከፈጸመበት ከጥቅምት 11 ቀን 2015ዓ.ም. ጀምሮ የተለመደውን ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ሲያካሂድ ሰንብቷል፡፡ ምልአተ ጉባኤው ለቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ እድገት ለሀገራችን ማኅበራዊና ልማታዊ ክንውን እንዲሁም ለመላው ሕዝባችን ሰላምና አንድነት ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፎአል፡፡

በዚሁ መሠረት፡-

  1. የዚሁ የጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መከፈቱን በማስመልከት የተደመጠው የመክፈቻ ንግግር
  • የሕዝባችንና የቤተ ክርስቲያናችን ሰላም ተጠብቆ እንዲኖር ማድረግ እንዲቻል፣
  • በሀገራችን በሰሜኑ ክልል በተከሠተው ጦርነት ምክንያት ከቀያቸው ስለተፈናቀሉና በአጠቃላይ በችግር ላይ ስለሚገኙ ወገኖቻችን መደረግ ስለሚገባው እገዛ፣
  • በቀጣይም የቤተ ክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ እድገት ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኰረ በመሆኑ ምልአተ ጉባኤው በዚሁ ላይ በስፋት ተነጋግሮ ለተግባራዊነቱ የሚመለከታቸው ሁሉ የበኩላቸውን እንዲወጡ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
  1. የ2015ዓ.ም. የመንበረ ፓትርያርክ ዓለም ዐቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ያሳለፈውን የጋራ መግለጫ በመመርመርና አስፈላጊ ማሻሻያዎችን በማድረግ የበጀት ዓመቱ የሥራ መመሪያ እንዲሆን ጉባኤው አጽድቋል፡፡
  2. የ2015ዓ.ም. የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የዓመቱን በጀት ድልድል አስመልክቶ ጉባኤው በስፋት ከተነጋገረ በኋላ የቀረበውን በጀት በማጽደቅ በሥራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
  3. ከ2007ዓ.ም. ጀምሮ በሥራ ላይ የነበረውን ሕገ ቤተክርስቲያን ወቅቱን በዋጀ መልኩ በማስጠናት መልካም አስተዳደርን ሊያሰፍን በሚችል ሁኔታ ተሻሽሎ በቀረበው ረቂቅ ላይ በመነጋገር ማሻሻያዎችን በማድረግ ረቂቅ ደንቡን አጽድቋል፡፡ በሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር በሥራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ካህናትና ምእመናን የሚያጋጥሟቸው ችግሮች ቀኖና ቤተክርስቲያንን በጠበቀ መልኩ በመንፈሳዊ ዳኝነት መታየትና ፍትሕ ማግኘት እንዲችሉ ለማስቻል በባለሙያ ተዘጋጅቶ የቀረበው የመንፈሳዊ ፍ/ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ በምልአተ ጉባኤ ጸድቋል፡፡ ከዚሁ ጋር ለቤተ ክርስቲያኒቱ ማኅበራዊና መንፈሳዊ የሥራ ሂደት ጠቃሚ የሆኑ ልዩ ልዩ ረቂቅ ደንቦችን መርምሮ በማጽደቅ በሥራ ላይ እንዲውሉ ወስኗል፡፡
  4. በቤተ ክርስቲያናችን ሕፃናትና አስተዳደግ ድርጅት አገልግሎት የሚገኘው ምግባረ ሠናይ ሆስፒታል በሙሉ ዐቅሙ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማስቻል የማሻሻያ ሥራ እንዲሠራ በተጨማሪም በቤተ ክርስቲያናችን በምሥራቅ አፍሪካ ውስጥ የመጀመሪያ የሆነ ታላቅ ሆስፒታል እንዲገነባ የቀረበውን ጥናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አጽድቋል፡፡
  5. በሀገራዊ ሰላምና አንድነት ላይ የተነጋገረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ሰላም ለሀገራችን ሕዝቦች አንድነትና ለቀጣይ በልማታዊ እድገት የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት መሠረት መሆኑን ሁሉም ተገንዝቦ ሀገራዊ ዕርቀ ሰላም እንዲወርድ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

ከዚሁም ጋር ሀገራዊ ሉዓላዊነትን በሚዳፈር መልኩ እየታየ ያለውን የውጭ መንግሥታት ጣልቃ ገብነት እንዲቆም ጉባኤው አሳስቧል፡፡

  1. በሰሜኑ ሀገራችንም ሆነ በውጭው ዓለም አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት የቤተ ክርስቲያናችን ማእከላዊ አሠራር ላይ እያሳዩት ያለው አካሄድ ለቤተ ክርስቲያናችንም ሆነ ለሀገራዊ አንድነታችን መጠበቅ ሲባል እንደገና በሰከነ መንፈስ ታይቶ ወደነባሩ ማእከላዊ አስተዳደርና አሠራር እንዲመለሱ ጉባኤው ጥሪውን ያቀርባል፡፡
  2. በቤተ ክርስቲያናችን ስብከተ ወንጌል እንዲስፋፋ መልካም አስተዳደር በሁሉም አቅጣጫ እንዲሰፍን ሀገራዊ አንድነትና ሰላም ተጠናክሮ እንዲቀጥል አህጉረ ስብከት ከምንግዜውም በላይ ተጠናክረው እንዲሠሩ ለማስቻል ምልአተ ጉባኤው በሰፊው መክሮ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
  3. የቤተ ክርስቲያኒቱ አእምሮኣዊ ሀብት ንብረትና የቱሪዝም ቅርሶቻችንን አስመልክቶ በቀረበው የባለሙያ ጥናት ላይ የተነጋገረው ምልአተ ጉባኤ ጥናቱን በማጽደቅ በተግባር እንዲተረጐም ወስኗል፡፡
  4. ሀገራችንን በልማት አሳድጎ ሕዝባችንን ከረኃብና ከድህነት ለማላቀቅ በማሰብ ግንባታው ከዓመታት በፊት ተጀምሮ በአሁኑ ጊዜ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ሕዝባችን እየተረባረበ ያለበት የዐባይ ግድብ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እስከሚደርስ በቤተ ክርስቲያናችንም ሆነ በሁሉም ዘንድ አስፈላጊው ድጋፍና ትብብር እንዲቀጥል ምልአተ ጉባኤው ጥሪ አቅርቧል፡፡
  5. እስከ አሁን ድረስ በቤተ ክርስቲያናችን የሚገኙ መንፈሳዊ ኮሌጆች ቊጥር ዝቅተኛ መሆኑን በመገንዘብና ለትምህርት አስፈላጊው ትኩረት እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶስ ባስቀመጠው አቅጣጫ ተጨማሪ ከሦስት ያላነሱ መንፈሳዊ ኮሌጆች መጨመራቸው ሥራም መጀመራቸውን ጉባኤው ተመልክቶ ኮሌጆቹ በቀጣይም በዕቅድና የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተምህሮ በጠበቀ መልኩ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝቧል፡፡
  6. ልማት ለቤተ ክርስቲያናችን ብሎም ለሀገራችን እድገት ለሕዝባችን የኑሮ መሻሻል በእጅጉ አስተዋፅኦው የጐላ መሆኑን በመገንዘብ በቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓመታዊ በዓላትን ለማክበር ለሚገኙ ምእመናን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሠረታዊ ልማት ለመተግበር እንዲቻል ጉባኤው ተነጋግሮ ለተግባራዊነቱ የወደፊት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
  7. ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተከሥ በነበረው ጦርነት ሀገራችንና ሕዝባችን ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ቤተ ክርስቲያናችንም የዚህ ችግር ገፈት ቀማሽ ሆና ካህናቶቿና ምእመናን ተከታዮቿ ለሞትና ለስደት መዳረጋቸው አብያተ ክርስቲያናት መፍረሳቸውና መቃጠላቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ሆኖም በአሁኑ ጊዜ ይኸው ጦርነት እንዲያበቃ ሀገራዊ ሰላምና አንድነት እንዲጠበቅ ትኵረት ባደረገ መልኩ በደቡብ አፍሪካ የተደረሰውን ስምምነት ቤተ ክርስቲያናችን በእጅጉ የምትደግፈውና በተደረሰው ስምምነት መሠረት ሰላሙ ፍጻሜ እንዲያገኝ የበኩሏን አስተዋፅኦ የምታበረክት ሲሆን ሁሉም አካል ለሰላሙ መገኘት በትኵረት እንዲሠራ ቅዱስ ሲኖዶስ በኦጽንዖት ያስገነዝባል፡፡ ይህ በቅዱስ ሲኖዶሱ ሁልጊዜም በጒጉት ሲጠበቅ፣ ጸሎት ሲጸለይበትና የሰላም ጥረት ሲደረግበት የቆየ በመሆኑ አሁንም በየአቅጣጫው ሀገራዊ ሰላም እንዲሰፍን ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
  8. በየአህጉረ ስብከቱ ያለውን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ክንውን የገመገመው ምልአተ ጉባኤ ለአብያተ ክርስቲያናት መልካም አስተዳደር እድገትና ለሰላም መስፈን ትኵረት በመስጠት በአንዳንድ አህጉረ ስብከት የብፁዓን አባቶች ዝውውርና ምደባ አድርጓል፡፡
  9. በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኙት የሶሪያ አንጾኪያ ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን የግብጽ አሌክሳንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንና የአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የቂልቅያ ሊባኖስ መንበር የሆኑት እነዚህ ሦስቱ አብያተ ክርስቲያናት በግብጽ ሀገር ከጥቅምት 8-10 በአውሮፓውያን አቈጣጠር ከኦክቶበር 18 እስከ 20 ድረስ ባካሄዱት የመሪዎች ጉባኤ በሰጡት መግለጫ በቅድሰት ሀገር ኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ገዳም ይዞታችን አስመልክቶ የሰጡት አሳዛኝ መግለጫ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በትኵረት ተመልክቶታል፡፡

እነዚሁ አብያተ ክርስቲያናት በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም የቤተ ክርስቲያናችን በሆነ የይዞታ ላይ የሰጡት የተሳሳተ መግለጫ የቤተ ክርስቲያናችንና የሀገራችንን ኢትዮጵያ ክብር የሚነካ ስለሆነ ጉባኤው በእጅጉ ተቃውሞታል፡፡ አብያተ ክርስቲያናቱም የሰጡትን መግለጫ መልሰው እንዲያጤኑትና የማረሚያ መግለጫ እንዲሰጡ የኢፌዲሪ መንግሥትም በጉዳዩ ጥብቅ ክትትል እንዲያደርግበት ጉባኤው ጥሪውን አቅርቧል፡፡

  1. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ከጥቅምት 21-27/2015 ዓ.ም. ድረስ ለሰባት ዕለታት ለምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ማስፈጸሚያ ባዘጋጀው የአንድ ሱባዔ የጸሎት ሳምንት፡-
    • ለሀገራችንና ብሎም ለዓለማችን ፍጹም ሰላም፣
    • ለሕዝቦች አንድነትና ሰላማዊ ኑሮ መገኘት፣
    • በጦርነት ምክንያት ከቄያቸው ለተፈናቀሉና
    • በልዩ ልዩ ወረርሽኝ በሽታ ለተያዙ ምሕረትና ጤና እንዲያገኙ፣

እንዲሁም በጦርነትና በማንኛውም አጋጣሚ ውድ ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስን እንዲሰጣቸው ሁሉን ቻይ ወደሆነው እግዚአብሔር በሱባዔ የሰነበተ ሲሆን በቀጣይም ለሀገራችንና ለሕዝባችን ፍጹም ሰላም መገኘት መላው ካህናትና ምእመናን በጸሎት እንዲተጉ ጉባኤው አሳስቧል፡፡

በመጨረሻም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በስብሰባ በሰነበተባቸው ዕለታት በቤተ ክርስቲያናችን የአጭርና የረጅም ጊዜ ዕቅድ ላይ በስፋት በመነጋገር መንፈሳዊ አገልግሎቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ልማታዊው ተግባር ትኵረት ተሰጥቶት እንዲከናወን ለኅብረተሰቡ ሊደረግ የሚገባው ማኅበራዊ ጉዳዮች አስፈላጊው ክትትል እንዳይለያቸው በተለይም በሀገራዊ ሰላምና አንድነት ላይ በሁሉም አካባቢዎች የተጠናከረ ሥራ እንዲሠራ በማስገንዘብ ከጥቅምት 11 ቀን 2015 እስከ ጥቅምት 25 ድረስ ሲያካሂድ የቆየውን ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጸሎት ዘግቷል፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ፤

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32022-11-04 10:25:512025-01-27 10:27:07ከጥቅምት 11 ቀን እስከ 25 ቀን 2015 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2015 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: ጥቅምት 12 ቀን 2015 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ጥቅምት 12 ቀን 2015 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ... Link to: መስከረም 16 ቀን 2016 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል የቅዱስነታቸው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: መስከረም 16 ቀን 2016 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል የቅዱስነታቸው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ መስከረም 16 ቀን 2016 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል የቅዱስነታቸው...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top