• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ነሐሴ 1 ቀን የ2006 ዓ.ም የጾመ ፍልሰታ መግቢያ ቃለ በረከት!

August 7, 2014

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

የተወደዳችሁ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትኖሩ ሕዝበ ክርስቲያን በአጠቃላይ እግዚአብሔር አምላክ እንኳን ለ2006 ዓ.ም ጾመ ማርያም በሰላም አደረሳችሁ፡፡

“ወዘሰ እንተ አንቀጽ ይበውእ ኖላዌ ዐባግዕ ውእቱ
በበሩ የሚገባ የበጎች እረኛ ነው።
(ዮሐ. 10፥2)

በብሉይ ኪዳን የበጎች እውነተኛ እረኛ እንደ ሆነ በብዙ ስፍራ የተነገረለት መሲሕ አንድ ቀን በዓለም እንደ ሚገለጽና በጎቹን በትክክል እንደ ሚጠብቅ በሕዝበ እግዚአብሔር ዘንድ የታወቀና የታመነ ነበረ። (ሕዝ. 34፥1-24)።

እግዚአብሔር ያስቀመጠው ቀመረ ዘመን ሲደርስ እውነተኛው እረኛ ክርስቶስ በተነገረለት በር በኩል ወደዚህ ዓለም መጣ፤ ይኸ በር የቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ማሕፀን ነበረ (ሕዝ. 44፥2-3)። በኦርቶዶክሱ ዓለምና በሌሎች ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት የምንገኝ ክርስቲያኖች ቅድስት ድንግል ማርያምን ከእግዚአብሔር በታች፣ ከፍጡራን በላይ፣ ከፍ አድርገን የምናከብርበት ዋና ምክንያት ድንግል ማርያም የዓለም መድኅን የክርስቶስ መግቢያ በርና ለሰው ልጅ የድኅነት ምክንያት ስለሆነች ነው፡፡

ከዚህም የተነሣ ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ የተነሡ ቅዱሳን ሊቃውንት ቅድስት ድንግል ማርያምን “አንቀጸ አድኅኖ ይእቲ አልባቲ ሙስና ማለትም ስሕተት ጥፋት የሌለባት የድኅነት በር ናት” ብለው በተደጋጋሚ ገልጸዋታል”፤ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቅ ቅዱስ ያሬድም በዜማ ድርሰቱ በዚህ ኀይለ ቃል ደጋግሞ አመስግኗታል፤ ቅድስት ድንግል ማርያም ለመድኀኒችን ለኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ በር በመሆኗ ክርስቲያን ለሆኑ ምእመናን ሁሉ እናት ናት፤ ጌታችን አምላካችንንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ እርስዋ የክርስቲያን እናት፣ እኛ ክርስቲያኖችም የእርስዋ ልጆች በማድረግ አስተሳስሮናል። (ዮሐ. 19፥26-27)

ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታችን በነገራቸው ቃል መሠረት ድንግል ማርያምን በእናትነት ተቀብለው በክብር ይከተሏት ነበር፡፡ ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይም ሥጋዋን ራሳቸው ቀብረው የበረከቷ ተካፋይ ለመሆን በነበራቸው ከፍተኛ ጒጉት ከነሐሴ 1 ቀን እስከ ነሐሴ 14 ቀን ሱባዔ ገብተው ፈጣሪን በጾምና በጸሎት ስለለመኑ ነሐሴ 14 ቀን የለመኑትን አግኝተው ሥጋዋን በጌቴሰሜኒ ቀብረዋል፤ ሆኖም በሦስተኛው ቀን ነሐሴ 16 ቀን ከመቃብር ተነሥታ ወደ ሰማያት ዐርጋለች፣ ቅዱሳን ሐዋርያትም ትንሣኤዋን በዐይን አይተው የበረከቷ ተካፋይ ሆነዋል፤ ይህንን ሐዋርያዊ ትምህርትና ትውፊት መነሻ በማድረግ በዓለም ያሉ ኦርቶዶክሳውያንና ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በየዓመቱ ከነሐሴ 1 ቀን እስከ 15 ቀን በመጾም ነሐሴ 16 ቀን በዓለ ትንሣኤዋን በታላቅ ድምቀት ያከብራሉ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም ሐዋርያዊትና ጥንታዊት እንደ መሆንዋ መጠን ከጥንት ጀምሮ ይህንን ክብረ ቅድስት ድንግል ማርያም ጠብቃ እስካሁን አቆይታለች፤ ለወደፊትም እስከ ዕለተ ምጽአት በዚሁ ይቀጥላል።

የቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ትንሣኤ ምክንያት አድርገን የምንጸመው ይህ ጾመ ማርያም ለሀገራችን፣ ለሕዝባችንና ለዓለሙ ሁሉ መዳንን፣ ምሕረትንና ይቅርታን ለማስገኘት ነው፡፡ የሃይማኖት ተልእኮ ምን ጊዜም ሰውን ማዳን እንጂ ሰውን ለጒዳት መዳረግ አይደለም፤ ሃይማኖት ተቀባይነትን ሊያገኝ ሊወደድና ሊከበር የሚችለው ለሰው ልጆች በሚሰጠው ክብርና የድኅነት አስተምህሮ ነው፤ ሃይማኖት ከእግዚአብሔር የተሰጠውን ተልእኮ በአግባቡ ማከናወን የሚችለው ሰላምን፣ እኩልነትን፣ መከባበርን፣ መረዳዳትን፣ ማስተዋልን ትዕግሥትንና ፍቅርን ማእከል አድርጎ ሲጓዝ ነው፡፡ ይህንን በሚቃረን መልኩ የሚጓዝ ሃይማኖት ባይኖርም የሃይማኖቱን ትክክለኛ አስተምህሮ በተሳሳተ መንገድ የሚተረጐሙና የሃይማኖትን ካባ ያጠለቁ ግለ ሰቦች በየሃይማኖቱ ውስጥ አይጠፉም፡፡ በሀገራችንም ሆነ በሌላው ክፍለ ዓለም የሰላምና የልማት ጠንቅ ሆነው ሰላማዊ ሕዝብንና እውነተኞች አማንያንን በማስቸገር የሚገኙት እንደነዚህ ያሉ ሰዎች ናቸው፡፡ ግለ ሰዎቹ የሃይማኖት ተልእኮ ፈጽሞ እንደ ሌላቸው ከምንም በላይ ግብራቸው ይመሰክርባቸዋል፤ ወደ ሃይማኖቱ መድረክ በእውነተኛው በር ሳይሆን በሌላ በር እየገቡ ከምንም በላይ ራሱን ሃይማኖቱን እየተገዳደሩት እንደሚገኙ ግልጽ ሆኖ ይታያል፡፡

ስለሆነም በበሩ ሳይሆን በሌላ መንገድ የሚገባ እርሱ እውነተኛ የበጎች እረኛ አይደለም (ዮሐ. 10፥1)፤ ብሎ ጌታችን ባስተማረን መሠረት እንደዚህ ዐይነታቸውን ግለሰቦች ነቅተን ልንከላከላቸው ይገባል፤ የሃይማኖት በሮች እምነት፣ ምግባር፣ መታዘዝ፣ ትሕትና፣ በሕግና በሥርዐት መኖር፣ ሰላም፣ አንድነት፣ ፍቅር፣ ስምምነት፣ መተሳሰብ፣ መከባበር፣ ሥራ መውደድ፣ ከተንኮልና ከአስመሳይነት መራቅ ናቸው፤ ከዚህ ውጭ የሚደረጉ የማስመሰል ተግባራት ሁሉ ማታለያ ከመሆን አልፈው የእውነተኛ ሃይማኖት መገለጫ ሊሆኑ አይችሉም፤

እግዚአብሔር ከላይ የተገለጹት የሃይማኖት መገለጫ ፍሬዎችን ይዘንና ከማናቸውም ግብረ ኀጢአት ርቀን እርሱን በመፍራትና ለእርሱ በመታዘዝ እንድንጾም ይፈልጋል፤ እንደዚሁም የተራበውን በማጒረስ፣ የታረዘውን በማልበስ፣ የተቸገረውን በመርዳት እንድንጾም ከወዲሁ በቂ ዝግጅት ማድረግ ይገባናል፤ እግዚአብሔር የመረጠው ጾም ይህ ነውና፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ ይቀድስ አሜን

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc2014-08-07 10:32:022024-12-05 10:33:05ነሐሴ 1 ቀን የ2006 ዓ.ም የጾመ ፍልሰታ መግቢያ ቃለ በረከት!
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ከግንቦት 6-19 ቀን 2006 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች Link to: ከግንቦት 6-19 ቀን 2006 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች ከግንቦት 6-19 ቀን 2006 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ... Link to: መስከረም 1 ቀን የ2007 ዓ.ም የዘመን መለወጫ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: መስከረም 1 ቀን የ2007 ዓ.ም የዘመን መለወጫ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ መስከረም 1 ቀን የ2007 ዓ.ም የዘመን መለወጫ ቃለ ምዕዳንና...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top