• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

ሚያዝያ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

May 6, 2015

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት
ምሕረትና ይቅርታ፣ ትዕግሥትና ቸርነት የባሕርዩ የሆነ እግዚአብሔር አምላክ፣ ሰፊውን የወርኀ ጾም አገልግሎት በሰላም አስፈጽሞ ብርሃነ ትንሣኤውን በሰላም ስለአሳየን፣ እንደዚሁም ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና ዓመታዊ ከሆነ ከዚህ የርክበ ካህናት ጉባኤ በሰላም ስላደረሰን ክብርና ምስጋና ለእርሱ እናቀርባለን፡፡

‹‹ኀበ ሀለዉ ክልኤቱ ወሠለስቱ ጉቡኣን በስምየ አነ እሄሉ ማእከሌሆሙ ህየ — ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እገኛለሁ።›› (ማቴ. 18÷20)

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ከዚህ በላይ በተጠቀሰው የጌታችን፣ የአምላካችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕያው ቃል ላይ የተመሠረተ እንደሆነ ሁላችንም እናውቃለን፡፡ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ጀማሪና ፈጻሚ ራሱ ጌታችን ቢሆንም ሥራው በአጠቃላይ በሰው ልጅ ድኅነት ላይ የሚከናወን ፍጹምና ምሉእ ተልእኮ በመሆኑ በአንድ ትውልድ ብቻ የሚያልቅ አይደለም፡፡

በመሆኑም ተልእኮው እስከ ዓለም መጨረሻ ለሚነሣው ትውልድ ሁሉ እንዲዳረስ፣ እርሱን ተከትለው የድኅነት አገልግሎት የሚሰጡ ሐዋርያት እንደሚያስፈልጉ ግልጽ ነበረ፡፡ ከዚህ አንጻር የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ የቅብብሎሽ ሥራ በመሆኑ እነሆ አባቶች ሲያልፉ በልጆች እየተተኩ ሥራው እኛ ዘንድ ደርሶአል፤ በዚህም ‹‹ወናሁ አነ እሄሉ ምስሌክሙ እስከ ኅልቀተ ዓለም፤ እነሆ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ›› (ማቴ. 28÷20) ብሎ የገባልን ቃል ኪዳን በተግባር እየተፈጸመልን አገልግሎታችን ከሀገር ውስጥ አልፎ መላውን ዓለም ባካለለ መልኩ እያካሄድን እንገኛለን፤ በዚህም እግዚአብሔርን እናመሰግነዋለን፡፡

ቤተ ክርስቲያናችን በሁሉም የዓለም ክልል ፈላጊዋ እየበረከተ መምጣቱ እግዚአብሔር በቤተ ክርስቲያናችን አማካኝነት ሊሠራ ያሰበው ሥራ እንዳለ የሚያመለክት ነው፤ ይህ ዕድል ለቤተ ክርስቲያናችን በጣም ትልቅ ስኬት የሚያስከትል በመሆኑ በሚገባ ልንሠራበትና ልንጠቀምበት ይገባል፡፡

በመሆኑም በውጭ ሀገራት የሚገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትና አገልጋይ ካህናት እንዲሁም መላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ኦርቶዶክሳዊ ቀኖናን ከመጠበቅ ጋር በሙሉ ኀላፊነት፣ በአንድነትና በኅብረት ሆነው በውጭ ሀገር ያለው የቤተ ክርስቲያናችንን ተልእኮ በማስፋፋትና በማጠናከር ረገድ አብዝተው እንዲሠሩ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ይጠበቅብናል፡፡

ከሀገር ውጭ ያሉት አብያተ ክርስቲያናት እየበረከቱ መምጣታቸው በአንድ በኩል የቤተ ክርስቲያናችን መጻኢ ዕድል ተስፋ ሰጭ እንደሆነ ሲያመለክት፣ በሌላ በኩል ደግሞ በቤተ ክርስቲያናችንም ሆነ በአጠቃላይ በኦርቶዶክሱ ዓለም የሌለ ገለልተኛ ነን የሚል ስም በመጠቀም ከእናት ቤተ ክርስቲያን መኮብለል ሊታረም የሚገባ እንደሆነ ያመለክታል፡፡

እንደ ቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና ካየነው “በሊቀ ጳጳስ ሥር ሆና የማትመራ ቤተ ክርስቲያን የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ናት ለማለት ያስቸግራል፡፡” በመሆኑም ያለጥንቃቄም እንበለው ያለ ማወቅ በፈጠረው መነሾ የተጀመረው ስሕተት ጊዜ ሊሰጠው ስለማይገባ በዚህ ዙሪያ እንደካሁን ቀደሙ ጠንክረን በማስተማርና በማስረዳት ወደ አንዲት ቤተ ክርስቲያን ጒያ ማሰባሰብ ይገባናል፤ ምእመናንም ይህንን ጊዜያዊ ስሕተት ለማስተካከል በሚደረገው ጥረት ተባባሪ እንዲሆኑ በዚህ አጋጣሚ ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

በሌላ በኩል በሀገር ውስጥ ያለችው ቤተ ክርስቲያን ከሰበካ ጉባኤ መቋቋም በኋላ ያሳየችው እመርታ በተለይም በትላልቅ ከተሞች እየታየ ያለው፡-
• በኢኮኖሚ የመለወጥ ሁናቴ፣
• የትምህርት ቤቶች በብዛት መገንባት፣
• የጤና ተቅዋማትና የምግባረ ሠናይ ድርጅቶችን ማቋቋም እየተለመደ መምጣት
• ወጣቶች በየሰንበት ት/ቤቱ ስለሃይማኖታቸው በቂ ዕውቀት መቅሰማቸው፣
• የስብከተ ወንጌል ሥራ እየሰፋና እየተወደደ መምጣቱ እጅግ ተስፋ ሰጭ ሆኖ ይገኛል፡፡

እነዚህ ተስፋ ሰጭ ተግባራት ያላቸውን ክፍተት በመሙላትና በማስተካከል ዘመኑ በሚጠይቀው ጥበብና ብልሀት ከሠራንባቸው የዕጥፍ ዕጥፍ ዕድገትን ማምጣት እንደምንችል ሁኔታዎች ያሳያሉ፤ ስለሆነም ለበለጠ እድገት የተሻለ አሠራርና የጋራ ተነሣሽነትን አንግበን በመሥራት እድገታችንን በፍጥነት እውን ማድረግ ጊዜው የሚጠይቀን ኀላፊነት ነው፡፡

ሁላችንም እንደምናውቀው ጥንካሬና ድክመት ምን ጊዜም ቢሆን የማይለያዩ አንጻራዊ ነገሮች ናቸውና በቤተ ክርስቲያናችን አሠራር ውስጥም ጥንካሬ እንዳለ ሁሉ ድክመትም እንደማይጠፋ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ በተለይም ካለፉት ዘመናት ጀምሮ እየተከሠተ ያለው የምእመናን ፍልሰት ወይም የበጎች መነጠቅና መኮብለል በመጀመሪያ ሊቀመጥ የሚገባ መሠረታዊ ችግር ሆኖ ይታያል፡፡

ሁኔታው በዚህ የሚቀጥል ከሆነ ከባድ ጥያቄ ሊያስነሣ የሚችል ጉዳይ መሆኑን ሁላችንም መገንዘብ አለብን፤ ስለሆነም ይህንን ችግር በወሳኝ መልኩ ለማስተካከል ጊዜ ሳይወስድ ይህ ቅዱስ ጉባኤ መፍትሔ ሊያበጅለት ይገባል፡፡

ሌላው በቤተ ክርስቲያናችን ተከታዮች እየተስተዋለ ያለው ችግር በስደትና በዝርወት የሚከሠት የሰብኣዊ መብት ጥሰትና የሃይማኖት ነፃነት እጦት፣ አልፎ ተርፎም ሕይወትን ማጣት ነው፤ ቤተ ክርቲያናችን በነዚህ ምክንያቶች የምታጣቸው ልጆች ቀላል ቊጥር ያላቸው አይደሉም፤ ልጆቻችን እንጀራ ፍለጋ ወደ ባዕድ ሀገር ሲሄዱ ስመ ክርስትና ከመለወጥ ጀምሮ ሃይማኖት እስከ መለወጥ የሚደርስ ተጽዕኖ ሁሉ እየገጠማቸው ብዙዎችን እያጣን ነው፤ ከዚህም ጋር በቅርቡ በሊቢያ እንደተከሠተው ያለ አረመኔያዊ ተግባር ክርስቲያን በመሆናቸው ብቻ እየተፈጸመባቸው ነው፡፡ የዚህ ሁሉ ማባባሻ ሆኖ የሚገኘው ሀገራችን ከድህነት ወጥታ በኢኮኖሚ ሌሎች ሀገሮች ከደረሱበት ደረጃ ባለመድረሷ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ምክንያቱም በሌላ ሀገር የሚገኘው ጥቅም በሀገር ውስጥ ቢገኝ ኖሮ ልጆቻችን ለስደት አይዳረጉም ነበር፤ ካልተሰደዱም ከላይ የተገለጸው ግፍና በደል በልጆቻችንና በቤተ ክርስቲያናችን አይደርስም ነበርና ነው፡፡

ስለሆነም አሁን በሀገራችንም ሆነ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ በአሸባሪዎች እየተፈጸመብን ያለው ተግዳሮት በወሳኝ መልኩ ለመመከት በሀገራችን ያለውን የልማትና የእድገት መርሐ ግብር ከሕዝቡ ጎን ተሰልፎ በማፋጠን ድህነትን ታሪክ ማድረግ ለነገ የማይባል የቤተ ክርስቲያናችን ተልእኮ ሊሆን ይገባል፡፡ ሆኖም ለብዙ ዘመናት ሥር ሰዶ የቆየው ድህነት በአንድ ጀምበር ይጠፋል ተብሎ ስለማይገመት “ከመሞት መሰንበት” የሚለውን አባባል በመከተልና አሁን ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ወጣት ልጆቻችን በሀገራቸው ሠርተው እንዲያድጉ ቤተ ክርስቲያናችን ያለማቋረጥ አዘውትራ ማስተማርና መምከር ይገባታል፤ እየመከረችም ትገኛለች፡፡

በመጨረሻም፤ ይህ ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በሚቀርቡ አጀንዳዎች መሠረት ለሰላም፤ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን የሚበጁ መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን በመፈተሸና በመመርመር ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በመወሰን ጉባኤውን እንዲያካሂድ በማሳሰብ የ2007 ዓ.ም. የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ዛሬ መከፈቱን እናበሥራለን፡፡

እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ፣ ይቀድስ አሜን

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/007-3.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32015-05-06 08:04:032024-12-07 08:12:15ሚያዝያ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ሚያዝያ 15 ቀን 2007 ዓ/ም፡ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጸሎተ ፍትሐት Link to: ሚያዝያ 15 ቀን 2007 ዓ/ም፡ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጸሎተ ፍትሐት ሚያዝያ 15 ቀን 2007 ዓ/ም፡ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት... Link to: ሚያዝያ 27 ቀን እስከ 30 ቀን 2007 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ Link to: ሚያዝያ 27 ቀን እስከ 30 ቀን 2007 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች፡፡ ሚያዝያ 27 ቀን እስከ 30 ቀን 2007 ዓ.ም የተካሄደው ቅዱስ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top