• Amharic  
  • English 
  • Home
  • Papal Messages
  • Biography
  • Patriarchs
  • Contact
  • Menu Menu

መስከረም 16 ቀን 2010 ዓ.ም. የመስቀል ደመራ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ

September 16, 2017

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
በሕመም ምክንያት በየጸበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤

ፍጥረታትን ሁሉ በጸጋው ፈጥሮ የሚመግብና የሚመራ መሐሪውና ይቅር ባዩ አምላካችን እግዚአብሔር ያለፈውን ዓመት በሰላም አስፈጽሞ ለአዲሱ የምሕረት ዓመት ስላደረሰን ፍጹም ክብር አምልኮትና ምስጋና ለእርሱ ይሁን፤ እንደዚሁም ለሁለት ሺሕ ዐሥር ዓመተ ምሕረት በዓለ መስቀል እንኳን በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!

“ወይመጽእ መዋዕለ ሣህል እምቅድመ ገጹ ለእግዚአብሔር
ከእግዚአብሔር ዘንድ የይቅርታ ዘመን ይመጣል፤”
(የሐዋ.ሥራ 3፥19)

ይቅርታ ከእግዚአብሔር የሚመነጭና ለዓለም ሁሉ ባለመቋረጥ የሚፈስ፣ ቀዋሚ የምሕረት ጅረት ነው፤ ሰማይ ከነግሡ ምድር ከነልብሱ በህልውና ጸንቶ ሊኖር የቻለውና የሚችለው በእግዚአብሔር ይቅርታ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ፍጥረት በበደለ ቊጥር ሳይቈጣ እግዚአብሔር በምሕረትና በይቅርታ ሁሉንም እያለፈ ፍጥረቱን ይመግባል፣ ይመራል፣ ያስተዳድራል፣ ይንከባከባል፤ የእግዚአብሔር ይቅርታ ሁሌ የማያቋርጥ ትልቅ ጸጋ ቢሆንም በመስቀል ላይ የገለጸው ይቅርታ ከሁሉም የላቀ ነው፡፡ ምክንያቱም በመስቀል ላይ የተፈጸመው ይቅርታ ጊዜያዊ ሳይሆን ዘለዓለማዊ በመሆኑ፣ እንዲሁ በነፃ የተሰጠ ሳይሆን መለኮት በተዋሐደው ደሙ የተገኘ በመሆኑ፣ በከፊል ሳይሆን ሰማያውያንንና ምድራውያንን ሁሉ በአንድነት ያጥለቀለቀ በመሆኑና ለወደፊትም የኀጢአት ሁሉ ማስተስረያ አድርጎ ያቆመው የይቅርታ ሕግ በመሆኑ በመስቀሉ ላይ የሆነው ይቅርታ ከይቅርታ ሁሉ ይበልጣል፡፡

በመስቀል ላይ የተፈጸመው የዕርቅና የይቅርታ ጸጋ ፊተኞቹንና ኋለኞቹን ሁሉ ያካተተ በመሆኑ ድንበር የለሽ ይቅርታ ነው፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ የእግዚአብሔር ይቅርታ ምድርን መላ፤ ሰማያትም በእግዚአብሔር ቃል ጸኑ፤ ኀይላቸውም ሁሉ ከአፉ እስትንፋስ የተገኘ ነው ብሎ የሚያስተምረን ይህንን ለመግለጽ ነው፡፡ (መዝ. 32፥6)

ቅዱስ ባስልዮስ ማርቶማ ጳውሎስ ሁለተኛ የሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ካቶሊኮስ፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጰሳትና ሜትሮፖሊታኖች፤
ክቡራንና ክቡራት የበዓሉ ተሳታፊዎች፤

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሌላው ክፍለ ዓለም በተሻለና በደመቀ ሁኔታ በዓለ መስቀልን የምታከብርበት ምክንያት እግዚአብሔር ለፍጡራኑ ከሠራው ሥራ ሁሉ ይልቅ በመስቀሉ የሠራው እጅግ የላቀና ሰውን ከሞተ ነፍስ የታደገ በመሆኑ ነው፡፡ ነገረ መስቀሉ ሁሉንም በእኩልነት ተቀብሎ ያስማማና አንድ ያደረገ፣ ሰላምንና ፍቅርን ያሰፈነ፣ በአምልኮተ ጣዖትና በብልሹ ሥነ ምግባር፣ በተሳሳተ እምነትና አስተሳሰብ ተበላሽቶ የነበረውን ዓለም ፍጹም ሰላማዊ ርትዓዊና ትሩፋዊ በሆነ ትምህርቱ ያጣፈጠ ነው፡፡

በዓለም ውስጥ የኢትዮጵያ ምእመናንን ያህል የመስቀልን ጣዕም የተገነዘበ የለም በሚያስብል ሁኔታ፣ ትእምርተ መስቀሉ በልብሳችን፣ በአካላችን፣ በቤታችን፣ በሥራ ዕቃዎቻችን፣ በጌጦቻችን፣ በዕለት ተዕለት ሥራችንና እንቅስቃሴአችን ሁሉ ሊኖር የቻለው፣ የቀደሙት ኢትዮጵያውያን አበው የመስቀሉን ጣዕም በነፍስ ወከፍ ኢትዮጵያዊ ኅሊና በሚገባ እንዲሠርጽ የሚያስችል ሥራ በመሥራታቸው እንደሆነ የማይካድ ነው፤ ለዚህም ማስረጃችን ጥዑም ለጒርዔየ ነገረ መስቀልከ የመስቀልህ ነገር ለጒረሮዬ ጣፋጭ ነው ብሎ ኢትዮጵያዊው ነባቤ መለኮት ቅዱስ ያሬድ ያስተማረው ትምህርት ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ትክክለኛውን መስቀል ከተቀበረበት ቦታ ከጎልጎታ በዛሬው ዕለት በተከሠተው ተኣምር ምክንያት እንዲወጣ ካደረገ በኋላ በሂደት ወደ ኢትዮጵያ ሀገራችን እንዲገባ ማድረጉ የኢትዮጵያውያንን ፍቅረ መስቀል አይቶ እንደሆነ ከሁኔታው መረዳት ይቻላል፤ በመሆኑም ኢትዮጵያን ከባዕድ ወራሪ፣ ከባዕድ አምልኮና ባህል የተጠበቀ፣ የነፃነት፣ የሃይማኖት፣ የአንድነት ኀይል የሆነ፣ በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ ኵሩና ጨዋ የሆነ ፣ ለማንም ይሁን ለማን ያልተበገረ ሕዝብ በዚህች ምድር በሚያስደንቅ ሁኔታ እንዲኖር ያደረገ፣ በሀገሪቱ መሐል ዙፋኑን ዘርግቶ የተቀመጠው የመስቀሉ ኀይል እንደሆነ ማንም ኢትዮጵያዊ ያውቃል፤ ዛሬ በዚህች ሰዓት በዚህ አደባባይ በተግባር እየገለጽነው ያለ ዐቢይ ትዕይንትም ይኸው ሐቅ ነው፡፡

ይህ ታላቅና በእግዚአብሔር በረከት የተመላ ሕዝብ በታቦተ ሕጉና በመስቀሉ ፊት ቆሞ ፈጣሪውን ሲለምን ያልተደረገለትና የማይደረግለት ኀይለ እግዚአብሔር የለም፡፡ በመሆኑም በየዓመቱ እንዲህ ባለ ሰልፍና ትዕይንት የምናከብረው የመስቀል በዓል ታማኙና ዘለዓለማዊው፣ ሁሉን ማድረግ የሚችል፣ የኀያላን ሁሉ ኀያል የሆነ አምላካችን እግዚአብሔር ይህንን ቅዱስ ሀገርና ሕዝብ ከሚታየውና ከማይታየው ፈተና እንዲጠብቅልን በጸሎትና በምስጋና በአንድነት ሆነን ለመማፀን ነው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ በመንፈሳዊ ኀይል በኩል የደከመችበት ጊዜ ፈጽሞ ባይኖርም በኢኮኖሚ ዐቅሟ ግን ወደኋላ የቀረችበት ጊዜ ቀላል እንዳልሆነ ሁላችንም የምናውቀው ነው፡፡ ምስጋና ለእግዚአብሔር ይሁንና በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዳር እስከ ዳር በቊርጠኝነትና በሀገር ወዳድነት ተንቀሳቅሶ ባስመዘገበው ልማትና እድገት ስማችን እንደገና እንደጥንቱ እየገነነ እንደመጣ ሁላችንም እያየን ነው፡፡ ዛሬ የሀገራችን ልማትና እድገት በየአቅጣጫው ተፋፍሞአል፣ ዛሬ በሂደት የሚገኘው የልማትና የእድገት ግስጋሤያችን የኢትዮጵያ ከፍታ እውን ሆኖ ቀድሞ የነበረው ገናና ስማችንና ሥልጣኔአችን እስኪረጋገጥ ድረስ አጠናክረን መቀጠል አለብን፡፡ ከዚህ አንጻር የዘንድሮውን በዓለ መስቀል የምናከብረው ይህ የነፍስ ወከፍ ኢትዮጵያዊ ቅዱስ ሕልም የሆነው ራእይ እውን እንዲሆን በመጸለይ ነው ፡፡

ቅዱስ ባስልዮስ ማርቶማ ጳውሎስ ሁለተኛ የሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ካቶሊኮስ፣
ብፁዓን ሊቃነ ጳጰሳትና ሜትሮፖሊታኖስ፣ክቡራን ክቡራት

የዘንድሮ የመስቀል በዓላችን ልዩ የሚያደርገው የሶስተኛ ሺሕ ወይም ሚሊኒየም ዐሥረኛ ዓመት የልማትና የእድገት ጒዞአችን በምናስብበት ወቅት፣ እንደዚሁም እጅግ በጣም ውድ እኅት የሆነችው የሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ካቶሊኮስ ቅዱስ ባስልዮስ ማርቶማ ጳውሎስ ሁለተኛ በተገኙበት እየተከበረ ያለ መሆኑ ነው፡፡ የቅዱስነታቸው ጒብኝት የመልካም ገጽታችን፣ የታላቅነታችን፣ የልማታችንና የሰላማችን አንዱ ማሳያ ነው፡፡ ሰላማችንንና አንድነታችንን ጠብቀን እስከተጓዝን ድረስ ፈላጊያችን አክባሪያችንና ወዳጃችን ብዙ ይሆናል፡፡ ሰላማችንን፣ አንድነታችንንና ወንድማማችነታችንን እንደ ዐይን ብሌን ጠብቀን ወደልማትና ሥራ ስንሰለፍ ብርቱዎች ነን፤ ስለዚህ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ግዳጅ ሰላምን መጠበቅ፣ ከበሽታ መራቅ፣ ልማትን ማፋጠን፣ እድገትን ማረጋገጥ ሊሆን ይገባል፡፡

በመጨረሻም፡ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በመሉ በአጽንዖት ለማስተላለፍ የምንፈልገው ዐቢይ መልእክት ሕዝባችን ከሁሉም በላይ የእግዚአብሔርን ድምፅ እርሱም “ ሰላም ለእናንተ ይሁን” የሚለውን ድምፅ ዘወትር እንዲሰማ ነው፤ ይህ ድምፅ የእድገቱና የድኅነቱ ዋስትና ነውና ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ ድምፁን ያለማመንታት ሰምቶና ተቀብሎ፣ ከበሽታ አምጪ ተግባራትና ከሁከት ርቆ “የአትዮጵያን ከፍታ” በቀጣዮቹ ዓመታት እንዲያረጋግጥ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡

መልካም የመስቀል በዓል ያድርግልን፤ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝባችንን ይባርክ ይቀድስ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/001-2-1000.jpg 664 1000 tc3 https://eotcp.org/e/wp-content/uploads/logo-en.svg tc32017-09-16 13:30:412025-01-28 13:31:52መስከረም 16 ቀን 2010 ዓ.ም. የመስቀል ደመራ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ
Search Search

Recent Posts

  • ሃይማኖተ እግዚአብሔር በኢትዮጵያ
  • የኢትዮጵያ መንበረ ፓትርያርክ እና ሐዋርያዊ የሥልጣነ ክህነት ትውፊት
  • የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው የዐቢይ ጾምን መግባት በማስመልከት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ አስተላልፈዋል
  • ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ
  • በቅዱስነታቸው ዘመነ ፕትርክና የተከናወኑና በታሪክ የሚዘከሩ ዐበይት ተግባራት፤

Archives

  • February 2025
  • December 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • March 2024
  • October 2023
  • September 2023
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • August 2022
  • June 2022
  • May 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
  • August 2021
  • May 2021
  • March 2021
  • January 2021
  • November 2020
  • October 2020
  • September 2020
  • August 2020
  • May 2020
  • April 2020
  • March 2020
  • February 2020
  • January 2020
  • November 2019
  • October 2019
  • September 2019
  • July 2019
  • June 2019
  • May 2019
  • April 2019
  • March 2019
  • January 2019
  • October 2018
  • September 2018
  • August 2018
  • July 2018
  • May 2018
  • April 2018
  • February 2018
  • January 2018
  • October 2017
  • September 2017
  • August 2017
  • July 2017
  • June 2017
  • May 2017
  • April 2017
  • March 2017
  • February 2017
  • January 2017
  • October 2016
  • September 2016
  • August 2016
  • June 2016
  • May 2016
  • April 2016
  • March 2016
  • January 2016
  • November 2015
  • October 2015
  • September 2015
  • August 2015
  • May 2015
  • April 2015
  • February 2015
  • January 2015
  • November 2014
  • October 2014
  • September 2014
  • August 2014
  • May 2014
  • April 2014
  • February 2014
  • January 2014
  • October 2013
  • September 2013
  • June 2013
  • May 2013
  • March 2013
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: መስከረም 1 ቀን 2010 ዓ.ም. የዘመን መለወጫ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ Link to: መስከረም 1 ቀን 2010 ዓ.ም. የዘመን መለወጫ በዓል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ መስከረም 1 ቀን 2010 ዓ.ም. የዘመን መለወጫ በዓል ቃለ... Link to: በ36ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ አሰተዳደር ጉባኤ ከጥቅምት 6-9 ቀን 2010 ዓ.ም አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ Link to: በ36ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ አሰተዳደር ጉባኤ ከጥቅምት 6-9 ቀን 2010 ዓ.ም አስመልከቶ የተሰጠ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፡፡ በ36ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top